የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

May 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል የመስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርቼ አስታወቁ።


በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ከ936 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የተገነባው የያዶት የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።


ፕሮጀክቱ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ከመቀነስ ባለፈ፤ ለእንስሳት የመጠጥ ውኃ አገልግሎት የሚውል መሆኑም ተመላክቷል።


አቶ ሮባ ቱርቼ በምረቃው ወቅት እንዳሉት፤ የክልሉ መንግሥት የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ በትኩረት እየሠራ ይገኛል።

መንግሥት የአርብቶ አደሩ ማኅበረሰብ በተደጋጋሚ ጊዜ የሚያጋጥመውን ድርቅ እንዲቋቋም በክልል ደረጃ ከ166 የሚበልጡ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ለአገልግሎት አብቅቷል ብለዋል።


ከተጠናቀቁት የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል 66 የሚሆኑት ለሰውና ለእንስሳት መጠጥ ጭምር አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸውንም አስረድተዋል።


በዛሬው ዕለት ለምረቃ የበቃው የያዶት የመስኖ ፕሮጀክት ከ3 ሺህ ሔክታር የሚበልጥ መሬት በማልማት ከ6 ሺህ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።


የባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አልይ በበኩላቸው፤ በዞኑ ቆላማ አካባቢዎች የተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርብቶ አደሩን ኑሮ በማሻሻል በኩል ከፍተኛ ውጤት እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።


በዞኑ ከ1 ሺህ 700 የሚበልጡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ከ4 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ተገንብተው እየተመረቁ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም ኅብረተሰቡን በቀጥታ ተጠቃሚ ለሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ እንደሚሰጥ አመላክተዋል።


የክልሉ መንግሥት የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለሚያረጋግጡ የልማት ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያረጋገጡት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መንግሥቱ በቀለ (ዶ/ር) ናቸው።


የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የቆላማና ዝናብ አጠር አካባቢዎች ዘላቂ ልማት ዕቅድ በመንደፍ የድርቅ ተጋላጭነትን ለመቋቋም በትጋት እየተሠራ ነው ብለዋል።


በቀጣይም የክልሉ መንግሥት ተመሳሳይ ፕሮጀክቶችን ለውጤት በማብቃት የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026