የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከተለያዩ ዞኖች እና ከጠምባሮ ልዩ ወረዳ ለተውጣጡ የልማት ጣቢያ ሠራተኞች ያዘጋጀው የግንዛቤ ማጎልበቻ ስልጠና በዱራሜ ከተማ እየተሰጠ ነው።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ወደልማት በመቀየር ከዘርፉ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ።

ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ እንደሆነ ያነሱት አቶ ኡስማን፣ ለዚህ ስኬትም የግብርና ልማት ጣቢያ ሠራተኞች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

የአካባቢውን ፀጋ ለይቶ በማልማት ረገድ በተሰራው ሥራ በርካታ አርሶ አደሮች ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸው፣ በዚህም አርሶ አደሮች ከራሳቸው ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል።

በተጨማሪም የኢንዱስትሪና የወጪ ምርቶችን በማምረት ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ነው የገለጹት።

በዘርፉ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ወጥነት ባለው መልኩ ለማጠናከር ለግብርና ልማት ጣቢያ ሠራተኞች የዛሬው የአቅም ግንባታ ስልጠና መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

ሠራተኞቹ ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸውም አቶ ኡስማን አሳስበዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቡቶ አኒቶ በበኩላቸው እንዳሉት፤ አርሶ አደሩን በቅርበት በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱ እንዲጨምር በማድረግ በኩል የግብርና ልማት ጣቢያ ሠራተኞች ሚና የጎላ ነው።

ቴክኖሎጂን ለአርሶ አደሩ በማሸጋገር፣ ግብርናን በማዘመንና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ የሚጠበቅባቸውን ሚና ማጠናከር እንዳለባቸውም አፈ ጉባኤው አሳስበዋል።

በመድረኩ ከከምባታ እና ከሀድያ ዞኖች እንዲሁም ከጠምባሮ ልዩ ወረዳ የተውጣጡ ከ1ሺህ 700 በላይ የልማት ጣቢያ ሠራተኞች እና የተለያዩ የሥራ ሀላፊዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026