🔇Unmute
ሚዛንአማን፣ነሐሴ18/2018(ኢዜአ):በደቡብምዕራብኢትዮጵያሕዝቦችክልልበተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኑሮውድነትንለማረጋጋትየተከናወኑ ተግባራትውጤታማመሆናቸውንየክልሉንግድናኢንቨስትመንትቢሮአስታወቀ።
ቢሮው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እያካሔደ ነው።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ በመድረኩ ላይ እንዳሉት፣ የንግድ ሚዛን ሥርዓትን በማስጠበቅ ጤናማ ግብይት መፍጠር ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ ይገኛል።
በዚህም በተጠናቀቀው የ2018 የበጀት ዓመት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚያስችሉ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን ይህም ውጤታማ እንደነበር ተናግረዋል።
ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመከላከል በተደረገው የክትትልና የቁጥጥር ሥራ 8 ሺህ በሚሆኑ ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።
ሕገ-ወጥ ንግድ የኑሮ ውድነትን የሚያባብስ መሆኑን ጠቅሰው፣ በተግባሩ ላይ በተገኙ ነጋዴዎች ላይ በተወሰደው እርምጃ ከ52 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ እንደተቻለ አቶ ታሪኩ ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል የቅዳሜና እሑድ ገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት ኑሮን ለማረጋጋት ያለውን አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት ወደ 36 ከፍ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ንግድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው መለሰ፣ ከተማ አስተዳደሩ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የቅዳሜና እሑድ ገበያ ማዕከላትን ማደራጀት መቻሉን ገልጸዋል።
የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በመንግሥት የተነደፉ ኢንሼቲቮችን በአግባቡ መሬት ላይ በማውረድ ሸማቹን ከአላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ መታደግ ትኩረት እንደተሰጠው ተናግረዋል።

በምዕራብ ኦሞ ዞን የጀሙ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ በረከት ደምሴ በበኩላቸው፣ በከተማዋ ያሉ ሁለት የግብይት ማዕከላትን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በማዕከላቱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ምርት የማቅረብ ሥራ እየተሠራ ሲሆን፣ የዋጋና ምርት መደበቅ ሕገ-ወጥ ተግባራት ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026
ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ። ...
Aug 19, 2026
ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...
Aug 19, 2026
ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...
Aug 11, 2026