🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦የደባርቅን የመልማት ፀጋ ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር ከተማዋን በመሰረተ ልማት ማበልጸግ እንደሚገባ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
የደባርቅን ከተማ ለማልማት የተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር "ደባርቅን እናሳምር ከተማችንን እናድምቅ" በሚል መሪ ሀሳብ በሂልተን ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሀብቶች ተገኝተዋል።
በገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ "ኑ ተፈጥሮ የገለጠችውን ድንቅ የቱሪስት መስህብ የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ በር የሆነችውን ደባርቅ ከተማ በጋራ እናልማ" የሚል ጥሪ ቀርቧል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ደባርቅ የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ ከተማ ናት።
ይሁን እንጂ ደባርቅ የታሪክ ባለቤትነቷን፣ የቱሪዝም መተላለፊያነቷን የሚመጥን ልማት አልታደለችም ብለዋል።
የደባርቅን የመልማት ፀጋ ወደ ተጨባጭ አቅም መለወጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩንም ጨምረው ገልጸዋል።
በመሆኑም ከተማዋን በማልማት የተፈጥሮ ውበቷን ለመግለጥ ሁሉም በጋራ ትብብር ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ ጌትነት ፀጋየ በበኩላቸው፤ ደባርቅ የቀድሞ የሰሜን አውራጃ ከተማ፣ በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መገኛ የቱሪዝም ቀዬ መሆኗን ገልጸዋል።
ደባርቅ በተፈጥሮ ሀብቶች የበለጸገች የቱሪዝም ማዕከል ብትሆንም የሚገባትን ያህል መልማት ባለመቻሏ የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ማራዘም አልቻለችም ነው ያሉት።
ስለሆነም መንግሥት ያመጣው የኮሪደር ልማት ተቋዳሽ እንድትሆን ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026
ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ። ...
Aug 19, 2026
ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...
Aug 19, 2026
ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...
Aug 11, 2026