አዲስ አበባ፤ ጥር 2/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍሎች ትናትን አመሻሽ የታዩት ቁሳዊ አካላት የቻይና ሺ ጂያን-19 (ShiJian-19) የተባለ ሳተላይት ቀሪ አካል ሊሆኑ እንደሚችል ያመለክታል ሲል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ አስታወቀ።
ሶሳይቲው በትናንቱ እንግዳ የሕዋ ክስተት ዙሪያ ከተለያዩ የሕዋ አካላት መከታተያ እና የመረጃ ቋቶች ያገኘናቸውን መረጃዎች በማጠናቀር ባደረግነው ጥልቅ ትንተና መሰረት ሳይንሳዊ መላምት ላይ መድረሱን ገልጿል።
በመረጃው መሰረት የሕዋ አካሉ ባለቤትነቱ የቻይና የሆነ ሺ ጂያን-19 (ShiJian-19) የተባለ ሳተላይት ቀሪ አካል ሊሆን እንደሚችል ያመላክታል ብሏል።
ሳተላይቱ መስከረም 17 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ምህዋር መወንጨፉንና ተልዕኮውን ጨርሶ ጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ መሬት መመለሱን አመልክቷል።
ነገር ግን ሳተላይቱ በተልዕኮው ላይ ሲገለገልባቸው የነበሩ የተለያዩ ክፍሎቹ ከዋናው ሳተላይት ተነጥለው በምህዋር ላይ ሲዞሩ መቆየታቸውን ነው ያስታወቀው።
ሶሳይቲው ለትንተናው የተጠቀመባቸው መረጃዎች ከሶስተኛ ወገን የመረጃ ቋቶች የተገኙ በመሆኑ የተረጋገጠ መረጃውን የሳተላይቱ ባለቤት ሃገር ቻይና እስክታረጋግጥ መጠበቅ እንደሚገባ ገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025