ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
በሐረር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሀገር አቀፍ ሕዝባዊ ኮንፍረንስ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸው የልማት፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና ሌሎች ስራዎች ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።
በተለይም ህዝብና መንግስትን በማስተባበር ሀገርን ማልማትና ማሻገር እንደሚቻል በግልጽ የታየበት መሆኑንም አመልክተዋል።
በሐረሪ ክልልም የተከናወኑ የልማት ስራዎች ነዋሪውን ተጠቃሚ ያደረጉና የህዝቡን የልማት ጥያቄ የመለሱ ናቸው ብለዋል።
መድረኩም ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውንና በቀጣይ በሚያከናውናቸው ስራዎች ላይ የህዝብ ድጋፍና ትብብር ለማጎልበት የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈም ያልተፈቱና ምላሽ ያላገኙ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና ሌሎች ስራዎችን ለመፍታት ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
በመድረኩ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበልን ጨምሮ በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እና የሐረሪ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025