
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
በሐረር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሀገር አቀፍ ሕዝባዊ ኮንፍረንስ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እንዳሉት ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸው የልማት፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና ሌሎች ስራዎች ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።

በተለይም ህዝብና መንግስትን በማስተባበር ሀገርን ማልማትና ማሻገር እንደሚቻል በግልጽ የታየበት መሆኑንም አመልክተዋል።
በሐረሪ ክልልም የተከናወኑ የልማት ስራዎች ነዋሪውን ተጠቃሚ ያደረጉና የህዝቡን የልማት ጥያቄ የመለሱ ናቸው ብለዋል።
መድረኩም ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውንና በቀጣይ በሚያከናውናቸው ስራዎች ላይ የህዝብ ድጋፍና ትብብር ለማጎልበት የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈም ያልተፈቱና ምላሽ ያላገኙ የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና ሌሎች ስራዎችን ለመፍታት ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
በመድረኩ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበልን ጨምሮ በብልፅግና ፓርቲ የአፋር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እና የሐረሪ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም ተገኝተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026