
አዲስ አበባ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- በዘንድሮው የበጋ የመስኖ ስንዴ ልማት እስካሁን 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሸን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ በበጋ ወራት የመኸር ሰብልን በአግባቡ በመሰብሰብ ብክነትን ለማሳቀረት እንዲሁም የበጋ መስኖ ልማትን ማጠናከር ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በ2016/2017 የመኸር ምርት ዘመን በዘር ከተሸፈነው 20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ቀናት ድረስ ብቻ በ18 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር ላይ የደረሰ ሰብል መሰብሰቡን ተናግረዋል።
ከዚህም 420 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል ነው ያሉት።
በዋና ዋና ሰብሎች በቆሎ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ ሩዝ እና አኩሪ አተር ከተሸፈነው 12 ነጥብ 17 ሚሊዮን ሄክታር መሬት 10 ነጥብ 6 ሚሊዮኑ መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህም 289 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አንስተዋል።
ወቅቱን የጠበቀ የግብርና ግብዓትን ተደራሽ ማድረግ፣ የክላስተር እርሻና የተቀናጀ የግብርና ስራ ለውጤታማነቱ ወሳኝ ሚና መጫወቱን ጠቅሰዋል።
እንደ ሀገር ለበጋ መስኖ ልማት በተሰጠው ትኩረት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ በበጋ ስንዴ ልማት 4 ነጥብ 27 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 172 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት እስካሁን የታረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታሩ በዘር መሸፈኑንና ሰብሉም በጥሩ ይዞታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የበጋ መስኖ ልማት ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የያዘችውን ግብ ለማሳካት ጥሩ መሰረት እየሆነ ነው ሲሉ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በበጋ ወራት የመስኖ ልማትን ለማስፋፋት ትላልቅ ግድቦች፣ የኤሌክትሪክ የመንገድ፣ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶች በመከናወን ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት።
የበጋ ወራት የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የከተማ ግብርና ሥራዎች በስፋት እየተተገበሩ መሆኑንም አስረድተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026