የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድልን የፈጠረ ነው - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ-ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሸን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ኢትዮጵያን ከብድር ጫና የሚያላቅቅ መሆኑን ሚኒስትሩ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡


ኢትዮጵያ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ መግባቷ ዘላቂ የልማት ፋይናንስ በመፍጠር ለበርካታ ዘርፎች መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል።


በሀገሪቱ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚን መፍጠር፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ሴክተሩን ማሻሻል እንዲሁም የዘርፎችን ምርታማነት በማሳደግ የመንግስትን የማስፈፀም አቅም መጨመር የማሻሻያው የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ አብራርተዋል።


የውጭ ምንዛሬ ዋጋ በገበያው እንዲተመን መደረጉ፣ አምራቾች የልፋታቸውን እንዲያገኙ እንዲሁም ኮንትሮባንድና መሰል ሕገ-ወጥ ተግባራት እንዲገቱ የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።


በዚህም የወጪ ንግድ እድገትን በታለመለት መልኩ ማስኬድ መቻሉን አንስተዋል።


ማሻሻያው የባንኮች የቁጠባ መጠን እንዲጨምር ማድረጉንም ጠቁመው፥ ብሔራዊ ባንክ ከቀደመው ጊዜ በበለጠ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እንዲኖረው ማስቻሉን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።


ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ ነው ብለዋል።


የወርቅ አምራቾች በዓለም አቀፍ የዋጋ ተመን በመሸጣቸው ወርቅን በኮንትሮባንድ ከመሸጥ ይልቅ ለማዕከላዊ ገበያ ለብሔራዊ ባንክ እንዲሸጡ መነሳሳት መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡


በዚህም ብሔራዊ ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የወርቅ መጠን በመግዛት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡


መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ፣ ለነዳጅ፣ ለዘይት፣ ለመሰረታዊ ሸቀጦች፣ ለመንግስት ሰራተኞች ደሞወዝ እና ለከተማ እና ገጠር ሴፍቲኔት የሚውል በዓመት ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ መንግስት ድጎማ ማድረጉን ተናግረዋል።


በቀጣይም ምርታማነትን ማሳድግ እና ማሻሻያውን በታለመለት መልኩ ማስኬድ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.