
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ-ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሸን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ኢትዮጵያን ከብድር ጫና የሚያላቅቅ መሆኑን ሚኒስትሩ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ መግባቷ ዘላቂ የልማት ፋይናንስ በመፍጠር ለበርካታ ዘርፎች መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል።
በሀገሪቱ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚን መፍጠር፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ሴክተሩን ማሻሻል እንዲሁም የዘርፎችን ምርታማነት በማሳደግ የመንግስትን የማስፈፀም አቅም መጨመር የማሻሻያው የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ አብራርተዋል።
የውጭ ምንዛሬ ዋጋ በገበያው እንዲተመን መደረጉ፣ አምራቾች የልፋታቸውን እንዲያገኙ እንዲሁም ኮንትሮባንድና መሰል ሕገ-ወጥ ተግባራት እንዲገቱ የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።
በዚህም የወጪ ንግድ እድገትን በታለመለት መልኩ ማስኬድ መቻሉን አንስተዋል።
ማሻሻያው የባንኮች የቁጠባ መጠን እንዲጨምር ማድረጉንም ጠቁመው፥ ብሔራዊ ባንክ ከቀደመው ጊዜ በበለጠ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እንዲኖረው ማስቻሉን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ ነው ብለዋል።
የወርቅ አምራቾች በዓለም አቀፍ የዋጋ ተመን በመሸጣቸው ወርቅን በኮንትሮባንድ ከመሸጥ ይልቅ ለማዕከላዊ ገበያ ለብሔራዊ ባንክ እንዲሸጡ መነሳሳት መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡
በዚህም ብሔራዊ ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የወርቅ መጠን በመግዛት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ፣ ለነዳጅ፣ ለዘይት፣ ለመሰረታዊ ሸቀጦች፣ ለመንግስት ሰራተኞች ደሞወዝ እና ለከተማ እና ገጠር ሴፍቲኔት የሚውል በዓመት ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ መንግስት ድጎማ ማድረጉን ተናግረዋል።
በቀጣይም ምርታማነትን ማሳድግ እና ማሻሻያውን በታለመለት መልኩ ማስኬድ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026