አዲስ አበባ፤ጥር 13/2017 (ኢዜአ)፦በተለያየ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ከ625 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ወደ ስራ መመለሳቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የእቅድ አፈፃፀም የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት እየተካሄደ ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የኢትዮጵያ ታምርት ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ በተለያየ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ከ625 በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ተመልሰዋል።
የአምራች ኢንዲስትሪዎች የማምረት አጠቃቀም 46 በመቶ የነበረ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መላኩ፥ ንቅናቄው ከተጀመረ አንስቶ በአማካይ የማምረት አቅም ወደ 61 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።
ንቅናቄው ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ በመንግስት ትኩረት እንዲያገኝና በዘርፉ ችግሮች ዙሪያ ተከታታይነት ያለው ውይይት በማድረግ ለችግሮቹ የመፍትሔ ባለቤት በመሆን በጋራ መስራት በመቻሉ የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች መተካት፣ በራስ ምርት የመኩራትና የመጠቀም ባህል እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በውይይቱ ላይ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አፈፃፀም መቅረቡን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025