
አዲስ አበባ፤ጥር 13/2017 (ኢዜአ)፦በተለያየ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ከ625 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ወደ ስራ መመለሳቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የእቅድ አፈፃፀም የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት እየተካሄደ ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንደገለፁት የኢትዮጵያ ታምርት ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ በተለያየ ምክንያት ስራ አቁመው የነበሩ ከ625 በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ተመልሰዋል።
የአምራች ኢንዲስትሪዎች የማምረት አጠቃቀም 46 በመቶ የነበረ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መላኩ፥ ንቅናቄው ከተጀመረ አንስቶ በአማካይ የማምረት አቅም ወደ 61 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል።

ንቅናቄው ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ በመንግስት ትኩረት እንዲያገኝና በዘርፉ ችግሮች ዙሪያ ተከታታይነት ያለው ውይይት በማድረግ ለችግሮቹ የመፍትሔ ባለቤት በመሆን በጋራ መስራት በመቻሉ የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች መተካት፣ በራስ ምርት የመኩራትና የመጠቀም ባህል እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በውይይቱ ላይ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አፈፃፀም መቅረቡን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026