የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በድሬዳዋ በግማሽ በጀት ዓመት ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ ፤ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦በድሬዳዋ በግማሽ በጀት ዓመት ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል ሲል የአስተዳደሩ ንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።

በኢንቨስትመንት ስራ ላይ ለመሰማራት ወደ ከተማዋ እየገቡ የሚገኙ ባለሃብቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የአስተዳደሩ ንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።

በዚህም በግማሽ በጀት ዓመት ብቻ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ አገራዊ የለውጥ ሪፎርሙን ተከትሎ መዋዕለ ነዋያቸውን በኢንቨስትመንት ስራ ላይ ለማዋል ከአገርና ከውጭ አገራት የሚመጡ ባለሃብቶች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል።

ድሬዳዋ ለጅቡቲ ወደብ ያላት ቅርበትና በመሠረተ ልማቶች መተሳሰሯ ድሬዳዋን ተመራጭ መዳረሻ ማድረጉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ታምርት አገራዊ የኢንዱስትሪ ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተደረገ የሚገኘው የተቀናጀ የመሠረተ ልማትና የፋይናንስ አቅርቦት፣ሙያዊ ድጋፍና ፈጣን አገልግሎቶች ወደ ስራ የሚገቡ ባለሀብቶች እንዲጨምር ማገዙን ነው የገለፁት።


እነዚህ ድጋፎች የተዘጉ እና በግንባታ ላይ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ማምረት እንዲገቡ ማስቻሉንም ጠቁመዋል።

በቢሮው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ጥናትና መረጃ ቡድን አስተባባሪ አቶ አበራ መንግስቱ በበኩላቸው፤ በግማሽ በጀት ዓመቱ የተደረጉ ድጋፎችና ምቹ አሠራሮች በመጠቀም ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል።


በማኑፋክቸሪንግ፣ በአገልግሎት፣በግብርናና በኮንስትራክሽን ዘርፎች የተሰማሩት ባለሃብቶቹ ወደ አገልግሎት ሲገቡ ከ34 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥሩም ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የፋይናንስ፣ የመሬት አቅርቦትና የግብዓት ችግሮች ከተቃለሉላቸው ግዙፍ ፋብሪካዎች አንዱ የተለያዩ የብረታ ብረት ውጤቶችን የሚያመርተው ድሬ ስቲል ፋብሪካ ተጠቃሽ ነው።

የፋብሪካው ስራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ዩሱፍ እንዳሉት፤ በአገር አቀፍና በድሬዳዋ አስተዳደር ለባለሃብቶች እየተደረገ ያለው ድጋፍ ተስፋ ሰጪ ስራዎችን ለመስራት አስችሏል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተደረገው የተቀናጀ ድጋፍና ከትትል ዘጠኝ የተዘጉና በግንባታ ላይ የቆዩ ፋብሪካዎች ወደ ማምረት እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን፤ ፋብሪካዎቹ ከ1 ሺህ 170 በላይ ሰዎች ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.