
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በትብብር መስራት በሚችሉባቸውን ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
የኩባንያዎቹ የስራ ኃላፊዎች በተለይም ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት መክረዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ ገልጸዋል።

የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እምቅ አቅም እንዳላት እና ለማልማት አመቺ መሆኗን እና በኢትዮጵያም ለዘርፉ ዕድገት የማማከር ስራ እንደሚያከናውን አመልክተዋል።
የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ከ75 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ ሃገራት ላይ ከ350 በላይ የሚሆኑ ሃገር አቀፍ ፕሮጀክቶችን በማማከርና ወደ ትግበራ በማስገባት ከ40 ዓመት በላይ የዘለቀ ልምድ ያለው ኩባንያ መሆኑን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026