የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በትብብር ለመስራት መከሩ</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በትብብር መስራት በሚችሉባቸውን ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

የኩባንያዎቹ የስራ ኃላፊዎች በተለይም ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት መክረዋል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ ገልጸዋል።


የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እምቅ አቅም እንዳላት እና ለማልማት አመቺ መሆኗን እና በኢትዮጵያም ለዘርፉ ዕድገት የማማከር ስራ እንደሚያከናውን አመልክተዋል።

የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ከ75 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ ሃገራት ላይ ከ350 በላይ የሚሆኑ ሃገር አቀፍ ፕሮጀክቶችን በማማከርና ወደ ትግበራ በማስገባት ከ40 ዓመት በላይ የዘለቀ ልምድ ያለው ኩባንያ መሆኑን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.