
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩትና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በትብብር መስራት በሚችሉባቸውን ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
የኩባንያዎቹ የስራ ኃላፊዎች በተለይም ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት መክረዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) የጃፓን ልማት ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳደግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ ገልጸዋል።

የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ፕሬዚዳንት ሾይቺ ካባያሽን (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እምቅ አቅም እንዳላት እና ለማልማት አመቺ መሆኗን እና በኢትዮጵያም ለዘርፉ ዕድገት የማማከር ስራ እንደሚያከናውን አመልክተዋል።
የጃፓን ዴቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ከ75 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ ሃገራት ላይ ከ350 በላይ የሚሆኑ ሃገር አቀፍ ፕሮጀክቶችን በማማከርና ወደ ትግበራ በማስገባት ከ40 ዓመት በላይ የዘለቀ ልምድ ያለው ኩባንያ መሆኑን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026