አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ልማትን ጨምሮ የገቢ አሰባሰብ አቅምን የማጎልበት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ የብሄራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ ኃይል አስታወቀ።
አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ እንዲገቡ ክትትል እንደሚደረግም ገልጿል።
የብሄራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ ኃይል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ በጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት ዛሬ አካሂዷል፡፡
ግብረ ኃይሉ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ከጉምሩክ ኮሚሽን በተወጣጡ ከፍተኛ ኃላፊዎች የሚመራ ነው።
በግምገማውም የበጀት ዓመቱ የገቢ አሰባሰብ በእቅዱ መሰረት በተሳካ ሁኔታ መፈጸሙን ግብረ ኃይሉ ገልጿል።
በቀሪ የበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በእቅድ የተያዘውን የገቢ እቅድ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አቅጣጫ አስቀምጧል።
ለገቢ አሰባሰቡ አጋዥ የሆኑ የስጋት ስራ አመራር ስርዓትን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የውዝፍ እዳ ክትትል ማጠናከር እና የጉምሩክ ዋጋን ወቅታዊ የማድረግ ስራ በቀጣይ ጊዜያት እንደሚከናወን አስታውቋል።
የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልማት ስራዎችን ማጠናከር፣ አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ እንዲገቡ ክትትል ማድረግ እንዲሁም የደረሰኝ እና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከርና ሌሎች የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
ግብረ ኃይሉ በታክስ አስተዳደሩ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚያስችሉ የታክስ ፖሊሲ፣ የሀገር ውስጥ ታክስ አስተዳደር እና በጉምሩክ ቀረጥና ታክስ አስተዳደር ጉዳዮች እቅድ በማዘጋጀት አፈፃፀሙን እየገመገመ እንደሚገኝም ከጉምሩክ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025