
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፡- ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ልማትን ጨምሮ የገቢ አሰባሰብ አቅምን የማጎልበት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ የብሄራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ ኃይል አስታወቀ።
አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ እንዲገቡ ክትትል እንደሚደረግም ገልጿል።
የብሄራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ ኃይል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ በጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት ዛሬ አካሂዷል፡፡
ግብረ ኃይሉ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ከጉምሩክ ኮሚሽን በተወጣጡ ከፍተኛ ኃላፊዎች የሚመራ ነው።
በግምገማውም የበጀት ዓመቱ የገቢ አሰባሰብ በእቅዱ መሰረት በተሳካ ሁኔታ መፈጸሙን ግብረ ኃይሉ ገልጿል።
በቀሪ የበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በእቅድ የተያዘውን የገቢ እቅድ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባም አቅጣጫ አስቀምጧል።
ለገቢ አሰባሰቡ አጋዥ የሆኑ የስጋት ስራ አመራር ስርዓትን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የውዝፍ እዳ ክትትል ማጠናከር እና የጉምሩክ ዋጋን ወቅታዊ የማድረግ ስራ በቀጣይ ጊዜያት እንደሚከናወን አስታውቋል።
የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልማት ስራዎችን ማጠናከር፣ አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ እንዲገቡ ክትትል ማድረግ እንዲሁም የደረሰኝ እና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ቁጥጥርና ክትትልን ማጠናከርና ሌሎች የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
ግብረ ኃይሉ በታክስ አስተዳደሩ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚያስችሉ የታክስ ፖሊሲ፣ የሀገር ውስጥ ታክስ አስተዳደር እና በጉምሩክ ቀረጥና ታክስ አስተዳደር ጉዳዮች እቅድ በማዘጋጀት አፈፃፀሙን እየገመገመ እንደሚገኝም ከጉምሩክ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026