የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ወጪያቸው ከ641 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የመጠጥ ውሃ ግንባታ እና የማማከር ኮንትራት አስተዳደር ውል ስምምነቶች ተፈረሙ</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከተለያዩ ተቋማት ጋር የመጠጥ ውሃ ግንባታ እና የማማከር ኮንትራት አስተዳደር ስራዎችን የተመለከቱ ሁለት የውል ስምምነቶች ተፈራርሟል።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እና የየተቋማቱ ተወካዮች ናቸው።

የመጀመሪያው ስምምነት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዋን ዋሽ ፕሮግራም የሚተገበረው የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አካል እንደሆነ ተገልጿል።

በዚህም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ የአጋም በር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ የእቃ አቅርቦትን ጨምሮ ከ631 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ ታውቋል።

የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከ21 ሺህ በላይ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እና በ18 ወራት ተገንብቶ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።


ሁለተኛው ስምምነት በሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ ለሚገነባው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የማማከርና ኮንትራት አስተዳደር ስራዎች ላይ ያተኮረ ነው።

አጠቃላይ ስራው 15 ወራት እንደሚቆይ እና ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበት ተመላክቷል።

የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ፍላጎት እንዲያሟሉ ማሳሰባቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.