
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከተለያዩ ተቋማት ጋር የመጠጥ ውሃ ግንባታ እና የማማከር ኮንትራት አስተዳደር ስራዎችን የተመለከቱ ሁለት የውል ስምምነቶች ተፈራርሟል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እና የየተቋማቱ ተወካዮች ናቸው።
የመጀመሪያው ስምምነት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዋን ዋሽ ፕሮግራም የሚተገበረው የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ የአጋም በር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ የእቃ አቅርቦትን ጨምሮ ከ631 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ ታውቋል።
የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከ21 ሺህ በላይ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እና በ18 ወራት ተገንብቶ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ሁለተኛው ስምምነት በሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ ለሚገነባው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የማማከርና ኮንትራት አስተዳደር ስራዎች ላይ ያተኮረ ነው።
አጠቃላይ ስራው 15 ወራት እንደሚቆይ እና ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበት ተመላክቷል።
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ፍላጎት እንዲያሟሉ ማሳሰባቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026