
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከተለያዩ ተቋማት ጋር የመጠጥ ውሃ ግንባታ እና የማማከር ኮንትራት አስተዳደር ስራዎችን የተመለከቱ ሁለት የውል ስምምነቶች ተፈራርሟል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እና የየተቋማቱ ተወካዮች ናቸው።
የመጀመሪያው ስምምነት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዋን ዋሽ ፕሮግራም የሚተገበረው የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ የአጋም በር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ የእቃ አቅርቦትን ጨምሮ ከ631 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ ታውቋል።
የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከ21 ሺህ በላይ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እና በ18 ወራት ተገንብቶ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ሁለተኛው ስምምነት በሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ ለሚገነባው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የማማከርና ኮንትራት አስተዳደር ስራዎች ላይ ያተኮረ ነው።
አጠቃላይ ስራው 15 ወራት እንደሚቆይ እና ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግበት ተመላክቷል።
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ በጥራት ተገንብተው የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ፍላጎት እንዲያሟሉ ማሳሰባቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026