የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባን ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ መዳረሻነት ከመቀየር ባለፈ የትኩረት ማዕከል አድርጓታል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱ መዲናዋን ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ መዳረሻነት ከመቀየር ባለፈ ይበልጥ የትኩረት ማዕከል እንድትሆን ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት የመንግሥትና የፓርቲ አፈፃፀም ግምገማ ተጠናቋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥የከተማ አስተዳደሩ አፈጻጸም የሚገመገመው ለህዝብ የገባነውን ቃል እና የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዳችንን ታሳቢ በማድረግ ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ለውጥ ሂደት ቢሆንም በሁሉም መመዘኛዎች ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተጨባጭ ሰው ተኮር ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡

አዲስ አበባ የነዋሪዎቿ፣የአፍሪካውያንና ዓለም አቀፋዊ ሀላፊነት ያለባት ከተማ መሆኗን የገለጹት ከንቲባዋ፤በስድስት ወራት ውስጥ የሚታይና የሚጨበጡ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡

የኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ከቱሪስት መተላለፊያነት ወደ መዳረሻነት ከመቀየር ባለፈ የዓለም የትኩረት ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል፡፡

በወንዞች ዳርቻ በተከናወነ ሥራ የወንዞችን መዓዛ መቀየር ጀምረናል ነው ያሉት፡፡

የኮሪደር ልማት የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ነዋሪዎች ማህበራዊ ትስስራቸው ተጠብቆ ከደሳሳ ጎጆ ወጥተው ደረጃውን ወደጠበቀ ቤት እንዲገቡ አስችሏል ብለዋል፡፡

የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ "መፍጠርና መፍጠን" ባህላችን ሊሆን ይገባል ሲባል በተመሳሳይ ጊዜና በጀት ወጥ አፈጻጸም ማስመዝገብ ጭምር መሆኑን አንስተዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት የኑሮ ጫናን መቀነስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር ሥራዎችን በብቃት መፈፀም ችሏል ብለዋል፡፡

በመዲናዋ ተማሪዎችን በቀን ሁለት ጊዜ በመመገብና የትምህርት ቤት ወጪያቸውን በመሸፈን ትውልድ ላይ አበክረን እየሰራን ነው ያሉት ከንቲባዋ።

የኢትዮጵያ ገበሬዎች በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከላት ምርታቸውን በመሸጥ የድካማቸውን ዋጋ የሚያገኙበት እድል ፈጥረናል ብለዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ በበኩላቸው፥ በመዲናዋ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ መስጠት እንደተጀመረ ገልጸው፥ ከነዋሪዎች ፍላጎትና ከተማዋ መድረስ ከሚገባት የከፍታ ደረጃ አንፃር ብዙ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ከነዋሪዎች ጋር በመተባበር በትራንስፖርት እና መሰል አገልግሎቶችና የመሰረተ ልማት ግንባታ ልማት በርብርብ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ፥ በመዲናዋ በተከናወኑ የልማት ስራዎች የተመዘገበው ውጤት ከነዋሪዎችም አልፎ ዓለም ዓቀፍ ተሞክሮ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡


በመሆኑም አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ውጥን ለማሳካት በሁሉም ዘርፎች ከዚህ በላይ የተቀናጀ የአመራር ጥረት ይጠይቃል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.