የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በክልሉ እስካሁን 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ተሸፍኗል- ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 02/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።

ጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።

የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በጨፌው መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንዳሉት በበጋ መስኖ ስንዴ 3 ነጥብ 32 ሚሊዮን ሄክታር የማሳ ዝግጅት ተደርግል።

በዚህም እስካሁን 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።

የክልሉ መንግሥት ለቡና፣ ሻይ ቅጠል እና ለአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው ለ2018 የሚተከል ከ839 ኪሎ-ግራም በላይ የሻይ ቅጠል ዘር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

ከቡና ችግኝ ዝግጅት አኳያም 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት እንክብካቤ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ባለፉት ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት መሰብሰቡን ነው የገለጹት።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅትን በተመለከተ በመደበኛ 173 ሜትር ኪዩቢክ ኮምፖስት እንዲሁም በትል አማካኝነት 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ማዘጋጀት መቻሉን አመልክተዋል።

የአፈር አሲዳማነት ለመቀነስ በተሰራው ስራም 63 ነጥብ 5 ኩንታል ኖራ ማዘጋጀት መቻሉንም ጠቁመዋል።

የተፈጥሮ ሃብቶችን በማልማት የቱሪዝም ገቢን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚህም ከ1 ሺህ 48 ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍኑ 6 የኢኮ-ቱሪዝም ቦታዎችን መለየት መቻሉንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.