
አዲስ አበባ፤ የካቲት 02/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
ጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በጨፌው መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንዳሉት በበጋ መስኖ ስንዴ 3 ነጥብ 32 ሚሊዮን ሄክታር የማሳ ዝግጅት ተደርግል።
በዚህም እስካሁን 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።
የክልሉ መንግሥት ለቡና፣ ሻይ ቅጠል እና ለአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው ለ2018 የሚተከል ከ839 ኪሎ-ግራም በላይ የሻይ ቅጠል ዘር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ከቡና ችግኝ ዝግጅት አኳያም 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት እንክብካቤ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት መሰብሰቡን ነው የገለጹት።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅትን በተመለከተ በመደበኛ 173 ሜትር ኪዩቢክ ኮምፖስት እንዲሁም በትል አማካኝነት 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ማዘጋጀት መቻሉን አመልክተዋል።
የአፈር አሲዳማነት ለመቀነስ በተሰራው ስራም 63 ነጥብ 5 ኩንታል ኖራ ማዘጋጀት መቻሉንም ጠቁመዋል።
የተፈጥሮ ሃብቶችን በማልማት የቱሪዝም ገቢን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም ከ1 ሺህ 48 ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍኑ 6 የኢኮ-ቱሪዝም ቦታዎችን መለየት መቻሉንም ተናግረዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026