
አዲስ አበባ፤ የካቲት 02/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጋ መስኖ ስንዴ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
ጨፌ ኦሮሚያ 4ኛ ዓመት 6ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ በጨፌው መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንዳሉት በበጋ መስኖ ስንዴ 3 ነጥብ 32 ሚሊዮን ሄክታር የማሳ ዝግጅት ተደርግል።
በዚህም እስካሁን 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።
የክልሉ መንግሥት ለቡና፣ ሻይ ቅጠል እና ለአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው ለ2018 የሚተከል ከ839 ኪሎ-ግራም በላይ የሻይ ቅጠል ዘር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ከቡና ችግኝ ዝግጅት አኳያም 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት እንክብካቤ እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የቡና ምርት መሰብሰቡን ነው የገለጹት።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅትን በተመለከተ በመደበኛ 173 ሜትር ኪዩቢክ ኮምፖስት እንዲሁም በትል አማካኝነት 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ማዘጋጀት መቻሉን አመልክተዋል።
የአፈር አሲዳማነት ለመቀነስ በተሰራው ስራም 63 ነጥብ 5 ኩንታል ኖራ ማዘጋጀት መቻሉንም ጠቁመዋል።
የተፈጥሮ ሃብቶችን በማልማት የቱሪዝም ገቢን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም ከ1 ሺህ 48 ሄክታር መሬት በላይ የሚሸፍኑ 6 የኢኮ-ቱሪዝም ቦታዎችን መለየት መቻሉንም ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026