የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በመስኖ ልማትና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ጉባኤ በአዲስ አበባ ይካሄዳል - የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በመስኖ ልማትና በአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችል ጉባኤ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ጉባኤው ከየካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ይህንኑ አስመልክቶ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ይገዙ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመከላከል በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።

ለአብነትም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የሌማት ትሩፋት፣ የውሃ አማራጭን የማስፋት ስራዎችን ጠቅሰዋል።

ጉባኤው የመስኖ ልማትን፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን መከላከል፣ ዓለም አቀፍ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን መቅሰም ዋነኛ ዓላማው መሆኑን አብራርተዋል።

ጉባኤው የመስኖ ልማትና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመቋቋም የሚያግዝ ተጨማሪ መዋዕለ ንዋይ ለማግኘት እንደሚረዳም ተናግረዋል።

በመድረኩ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ የዘርፉ የስራ ሃላፊዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ተጋባዠ እንግዶችና ከ1 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ይገኙበታል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያከናወነቻቸው ተግባራት በተለይም በስንዴ ልማት ዙሪያ ያላትን ልምድ እንደምታጋራም ገልጸዋል።

እንዲሁም በዘርፉ ቴክኖሎጂያዊ አሰራሮችን ማጎልበት፣ አካታችነትንና አሳታፊነትን ማረጋገጥና የመንግስትና የግል አጋርነትን ማጠናከር ሌላኛው የጉባኤው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.