
አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በመስኖ ልማትና በአየር ንብረት ለውጥ ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችል ጉባኤ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ጉባኤው ከየካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህንኑ አስመልክቶ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ይገዙ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመከላከል በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
ለአብነትም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የሌማት ትሩፋት፣ የውሃ አማራጭን የማስፋት ስራዎችን ጠቅሰዋል።
ጉባኤው የመስኖ ልማትን፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን መከላከል፣ ዓለም አቀፍ ልምዶችንና ተሞክሮዎችን መቅሰም ዋነኛ ዓላማው መሆኑን አብራርተዋል።
ጉባኤው የመስኖ ልማትና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽእኖን ለመቋቋም የሚያግዝ ተጨማሪ መዋዕለ ንዋይ ለማግኘት እንደሚረዳም ተናግረዋል።
በመድረኩ ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ የዘርፉ የስራ ሃላፊዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ተጋባዠ እንግዶችና ከ1 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ይገኙበታል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያከናወነቻቸው ተግባራት በተለይም በስንዴ ልማት ዙሪያ ያላትን ልምድ እንደምታጋራም ገልጸዋል።
እንዲሁም በዘርፉ ቴክኖሎጂያዊ አሰራሮችን ማጎልበት፣ አካታችነትንና አሳታፊነትን ማረጋገጥና የመንግስትና የግል አጋርነትን ማጠናከር ሌላኛው የጉባኤው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑንም አብራርተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026