
ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር)፤ የብልፅግና ፓርቲ በ2ኛ መደበኛ ጉባኤው ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ለስራ እድል ፈጠራ የተሰጠውን ትኩረት በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ መሰረት በማድረግ በክለሉ ለስራ እድል ፈጠራ በቅንጅትና በልዩ ትኩረት ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በማኑፋክቸሪግ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በሌሎችም መስኮች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጨምረው አንስተዋል።
የዜጎችን በተለይም የወጣቶችን ክህሎት በማጎልበትና በማሰልጠን በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር የሚደረገው ትብብር የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ በመከተል በክልሉ ለ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እደል መፍጠር መቻሉን አስታውሰው ለቀጣይ ስራዎች የተሻለ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል።
ለእቅዱ ማሳካትም የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ የባለሃብቶችና የአጋር አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026