የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ይሰራል - የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር)፤ የብልፅግና ፓርቲ በ2ኛ መደበኛ ጉባኤው ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ለስራ እድል ፈጠራ የተሰጠውን ትኩረት በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ መሰረት በማድረግ በክለሉ ለስራ እድል ፈጠራ በቅንጅትና በልዩ ትኩረት ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በማኑፋክቸሪግ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በሌሎችም መስኮች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጨምረው አንስተዋል።

የዜጎችን በተለይም የወጣቶችን ክህሎት በማጎልበትና በማሰልጠን በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር የሚደረገው ትብብር የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

በመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ በመከተል በክልሉ ለ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እደል መፍጠር መቻሉን አስታውሰው ለቀጣይ ስራዎች የተሻለ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በክልሉ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል።

ለእቅዱ ማሳካትም የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ የባለሃብቶችና የአጋር አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.