
ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር)፤ የብልፅግና ፓርቲ በ2ኛ መደበኛ ጉባኤው ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ለስራ እድል ፈጠራ የተሰጠውን ትኩረት በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ መሰረት በማድረግ በክለሉ ለስራ እድል ፈጠራ በቅንጅትና በልዩ ትኩረት ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በማኑፋክቸሪግ፣ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በሌሎችም መስኮች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጨምረው አንስተዋል።
የዜጎችን በተለይም የወጣቶችን ክህሎት በማጎልበትና በማሰልጠን በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር የሚደረገው ትብብር የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የተቀመጠውን አቅጣጫ በመከተል በክልሉ ለ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እደል መፍጠር መቻሉን አስታውሰው ለቀጣይ ስራዎች የተሻለ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ይሰራል ብለዋል።
ለእቅዱ ማሳካትም የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ የባለሃብቶችና የአጋር አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026