የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መጥቷል - አምባሳደር ብርቱካን አያኖ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ፡፡

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እና 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የእንግዶች አቀባበል መርሃግብር የብሔራዊ ኮሚቴ ሰብሳቢና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በተገኙበት በማርች ባንድና በሌሎች የጎዳና ላይ ትርኢቶች በደመቀ መልኩ ተጀምሯል።

በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በተሳካ መልኩ ለማስተናገድ አብይ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውቀዋል፡፡


አብይ ኮሚቴው 35 ተቋማትን የያዘ ብሄራዊ ኮሚቴ በማዋቀር የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡

ጉባኤውን አስመልክቶ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማትና ለሚመለከታቸው አካላት በቂ ስልጠና መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም እንግዶቹን በተሟላ መልኩ የሚያስተናግዱ በጎ ፍቃደኞችን ጨምሮ ለሆቴሎች፣ ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ለአሽከርካሪዎች በቂ ስልጠና በመስጠት ለጉባኤው ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ነው ያስረዱት፡፡

አዲስ አበባ እንግዶቿን ለመቀበል ውብና ጽዱ ሆና እየተጠባበቀች መሆኗን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በጉባኤው ከ11 ሺህ ያላነሱ እንግዶች እንደሚጠበቁ አስታውቀዋል፡፡

ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶች ስለ ኢትዮጵያ ጥልቅ መረጃን እንዲያገኙ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ ስፍራዎችንና የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ ይደረጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለጉባኤው በዓለም መድረክ ስሟን ከፍ አድርጎ የሚያስጠራ ዝግጅት ማድረጓንም አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.