
አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ፡፡
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እና 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የእንግዶች አቀባበል መርሃግብር የብሔራዊ ኮሚቴ ሰብሳቢና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በተገኙበት በማርች ባንድና በሌሎች የጎዳና ላይ ትርኢቶች በደመቀ መልኩ ተጀምሯል።
በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በተሳካ መልኩ ለማስተናገድ አብይ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውቀዋል፡፡

አብይ ኮሚቴው 35 ተቋማትን የያዘ ብሄራዊ ኮሚቴ በማዋቀር የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡
ጉባኤውን አስመልክቶ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማትና ለሚመለከታቸው አካላት በቂ ስልጠና መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንግዶቹን በተሟላ መልኩ የሚያስተናግዱ በጎ ፍቃደኞችን ጨምሮ ለሆቴሎች፣ ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ለአሽከርካሪዎች በቂ ስልጠና በመስጠት ለጉባኤው ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ነው ያስረዱት፡፡
አዲስ አበባ እንግዶቿን ለመቀበል ውብና ጽዱ ሆና እየተጠባበቀች መሆኗን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በጉባኤው ከ11 ሺህ ያላነሱ እንግዶች እንደሚጠበቁ አስታውቀዋል፡፡
ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶች ስለ ኢትዮጵያ ጥልቅ መረጃን እንዲያገኙ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ ስፍራዎችንና የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ ይደረጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለጉባኤው በዓለም መድረክ ስሟን ከፍ አድርጎ የሚያስጠራ ዝግጅት ማድረጓንም አስታውቀዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026