
አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ፡፡
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እና 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የእንግዶች አቀባበል መርሃግብር የብሔራዊ ኮሚቴ ሰብሳቢና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በተገኙበት በማርች ባንድና በሌሎች የጎዳና ላይ ትርኢቶች በደመቀ መልኩ ተጀምሯል።
በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በተሳካ መልኩ ለማስተናገድ አብይ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውቀዋል፡፡

አብይ ኮሚቴው 35 ተቋማትን የያዘ ብሄራዊ ኮሚቴ በማዋቀር የተሟላ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ የማስተናገድ አቅሟ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል፡፡
ጉባኤውን አስመልክቶ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማትና ለሚመለከታቸው አካላት በቂ ስልጠና መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡
በዚህም እንግዶቹን በተሟላ መልኩ የሚያስተናግዱ በጎ ፍቃደኞችን ጨምሮ ለሆቴሎች፣ ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ለአሽከርካሪዎች በቂ ስልጠና በመስጠት ለጉባኤው ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ነው ያስረዱት፡፡
አዲስ አበባ እንግዶቿን ለመቀበል ውብና ጽዱ ሆና እየተጠባበቀች መሆኗን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በጉባኤው ከ11 ሺህ ያላነሱ እንግዶች እንደሚጠበቁ አስታውቀዋል፡፡
ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶች ስለ ኢትዮጵያ ጥልቅ መረጃን እንዲያገኙ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ ስፍራዎችንና የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ ይደረጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ለጉባኤው በዓለም መድረክ ስሟን ከፍ አድርጎ የሚያስጠራ ዝግጅት ማድረጓንም አስታውቀዋል፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026