አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት ጉባኤን ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን ኢትዮጵያ እሴቶች እና የቱሪስት መስህቦችን ለማስተዋወቅ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የቱሪዝምና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን ገለፀ።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹና ውብ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚረዳቸውም ተገልጿል።
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን እንግዶችን ለመቀበል ሁለንተናዊ ዝግጅት መጠናቀቁም ተጠቁሟል።
ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አስጎብኝ ድርጅቶችና ሆቴሎች የህብረቱ ጉባኤን ለመካፈል ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመዋል።
የቱሪዝም እና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን የፕሮጀክት ማኔጂንግ ዳይሬክተር አስማ መፍቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ አዲስ አበባ ውስጥ ሆቴሎች እንደየ ደረጃቸው እንግዶቻቸውን ለማስተናገድ ዝግጅት አጠናቀዋል።
በተለይም የኢትዮጵያን ባሕላዊ እሴቶች የሚያስተዋውቁ ምግቦች፣ አልባሳት፣ ባህላዊ እሴቶችና ሌሎች የቱሪስት መስህቦችን በፓኬጅ ደረጃ ቀርጾ ለማስተዋወቅ ዝግጅት መደረጉንም እንዲሁ።
ጉባኤው በአዲስ አበባ ውስጥ መካሔዱ በዋናነት የቱሪዝምና ሆቴል ዘርፉን ይበልጥ ለማስተዋወቅ ሰፊ እድል የሚፈጥር መሆኑንም ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚያግዝም ተገልጿል።
በዋናነትም በቅርቡ በመዲናዋ የተገነቡ መናፈሻዎችና ፓርኮችን ለማስጎብኝትም ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውም የእንግዶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም የሚያስችሉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025