
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት ጉባኤን ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን ኢትዮጵያ እሴቶች እና የቱሪስት መስህቦችን ለማስተዋወቅ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የቱሪዝምና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን ገለፀ።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹና ውብ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚረዳቸውም ተገልጿል።
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን እንግዶችን ለመቀበል ሁለንተናዊ ዝግጅት መጠናቀቁም ተጠቁሟል።

ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አስጎብኝ ድርጅቶችና ሆቴሎች የህብረቱ ጉባኤን ለመካፈል ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመዋል።
የቱሪዝም እና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን የፕሮጀክት ማኔጂንግ ዳይሬክተር አስማ መፍቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ አዲስ አበባ ውስጥ ሆቴሎች እንደየ ደረጃቸው እንግዶቻቸውን ለማስተናገድ ዝግጅት አጠናቀዋል።
በተለይም የኢትዮጵያን ባሕላዊ እሴቶች የሚያስተዋውቁ ምግቦች፣ አልባሳት፣ ባህላዊ እሴቶችና ሌሎች የቱሪስት መስህቦችን በፓኬጅ ደረጃ ቀርጾ ለማስተዋወቅ ዝግጅት መደረጉንም እንዲሁ።
ጉባኤው በአዲስ አበባ ውስጥ መካሔዱ በዋናነት የቱሪዝምና ሆቴል ዘርፉን ይበልጥ ለማስተዋወቅ ሰፊ እድል የሚፈጥር መሆኑንም ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚያግዝም ተገልጿል።
በዋናነትም በቅርቡ በመዲናዋ የተገነቡ መናፈሻዎችና ፓርኮችን ለማስጎብኝትም ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውም የእንግዶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም የሚያስችሉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026