
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት ጉባኤን ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን ኢትዮጵያ እሴቶች እና የቱሪስት መስህቦችን ለማስተዋወቅ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የቱሪዝምና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን ገለፀ።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹና ውብ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚረዳቸውም ተገልጿል።
38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም 46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን እንግዶችን ለመቀበል ሁለንተናዊ ዝግጅት መጠናቀቁም ተጠቁሟል።

ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል አስጎብኝ ድርጅቶችና ሆቴሎች የህብረቱ ጉባኤን ለመካፈል ለሚመጡ እንግዶች ቀልጣፋና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመዋል።
የቱሪዝም እና ሆቴል ማርኬት አሶሴሽን የፕሮጀክት ማኔጂንግ ዳይሬክተር አስማ መፍቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ አዲስ አበባ ውስጥ ሆቴሎች እንደየ ደረጃቸው እንግዶቻቸውን ለማስተናገድ ዝግጅት አጠናቀዋል።
በተለይም የኢትዮጵያን ባሕላዊ እሴቶች የሚያስተዋውቁ ምግቦች፣ አልባሳት፣ ባህላዊ እሴቶችና ሌሎች የቱሪስት መስህቦችን በፓኬጅ ደረጃ ቀርጾ ለማስተዋወቅ ዝግጅት መደረጉንም እንዲሁ።
ጉባኤው በአዲስ አበባ ውስጥ መካሔዱ በዋናነት የቱሪዝምና ሆቴል ዘርፉን ይበልጥ ለማስተዋወቅ ሰፊ እድል የሚፈጥር መሆኑንም ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
በመዲናዋ የተካሔደው የኮሪደር ልማት ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶችን ምቹ በሆነ መንገድ ከማስተናገድ ባለፈ የንግድ እንቅስቃሴን ለማፋጠን እንደሚያግዝም ተገልጿል።
በዋናነትም በቅርቡ በመዲናዋ የተገነቡ መናፈሻዎችና ፓርኮችን ለማስጎብኝትም ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውም የእንግዶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም የሚያስችሉ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026