የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርግ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርግ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

በጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።

ርዕሰ መስተዳድሯ በልማቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንዳሉት የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው።


በተለይም የከተሞችን ገፅታ ከመቀየርና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።

የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የዲዛይንና የጥናት ስራው ባለፉት ሶስት ወራት ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው፤ ዛሬ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መሸጋገሩን ገልፀዋል።

በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡ ሁለንተናዊ ድጋፍና ቀና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሯ አስገንዝበዋል።


የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ርዕሰ በከተማ ጋምቤላ የሚከናወነው የኮርደር ልማት የከተማውን ማስተር ፕላን መሠረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በማቀናጀት የሚተበገር ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።

የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ከ14 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው አራት ዋና ዋና መንገዶችን ለማልማትና ለማስዋብ ግብ ተጥሎ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል።

በዚህም መሠረት ከአቦቦ ኬላ እስከ ባሮ ድልድይ፣ ከስላሴ እስከ ዶቦስኮ፣ ከአደባባይ እስከ ዲፖ እና ከአደባባይ ቄራ መስመር በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ከ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሚተገበር አብራርተዋል።

የኮሪደር ልማቱ ሲጠናቀቅ የጋምቤላ ከተማን ይበልጥ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ከማድረግ ባለፉ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ አካባቢን ለመፍጠር ያስችላል ሲሉም ከንቲባው አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.