
አዲስ አበባ፤ የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ችግሮችን በመቋቋም ዕድገቷን እንድታፋጥን ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።
46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በስብሰባው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የአፍሪካ የወደፊት እጣ ፋንታ በጋራ ፈቃደኝነት እና ተግባር ላይ የተመሰረተ ነው ብለዋል።
መጪውን ጊዜ በስኬት ለመወጣት ትብብር ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ አፍሪካ ችግሮችን በመቋቋም ዕድገቷን ማፋጠን እንድትችልም ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የአፍሪካ ሕብረት 2063 አጀንዳን ለማሳካት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን በእጥፍ ማሳደግ እንደሚያስፈልግም እንዲሁ።
የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ስብሰባው ለመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችና ሌሎች ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026