የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለወረዳ ማዕከላት መድረሱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በዞኑ የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት የምርት ግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ታሲሳ እንዳሉት በምርት ዘመኑ 251 ሺህ 340 ኩንታል አፈር ማዳበሪያ ለዞኑ አርሶአደሮች ይቀርባል።
ዘንድሮ የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 50 ሺህ ኩንታል ብልጫ እንዳለው ገልጸው፤ በእስከሁኑ ሂደትም 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በዞኑ በሚገኙ የወረዳ ማዕከላት መግባቱን አመልክተዋል፡፡
በቀሩት ጊዜያት የአፈር ማዳበሪያውን በማጓጓዝ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ለማድረስ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
የግብዓት አቅርቦትና ስርጭቱም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ የሚካሄድ በመሆኑ በፊት የነበሩትን አሰራር ችግሮች ከመቅረፍ ባለፈ አርሶ አደሩ ለእርሻ ልማት ስራው ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲያገኝ እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡
የዞኑ አርሶ አደሮች በአቅራቢያቸው በሚገኘው የማዳበሪያ ማሰራጫ ማዕከላት ተገኝተው በጊዜ መውሰድ እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025