
የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለወረዳ ማዕከላት መድረሱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በዞኑ የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት የምርት ግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ታሲሳ እንዳሉት በምርት ዘመኑ 251 ሺህ 340 ኩንታል አፈር ማዳበሪያ ለዞኑ አርሶአደሮች ይቀርባል።
ዘንድሮ የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 50 ሺህ ኩንታል ብልጫ እንዳለው ገልጸው፤ በእስከሁኑ ሂደትም 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በዞኑ በሚገኙ የወረዳ ማዕከላት መግባቱን አመልክተዋል፡፡

በቀሩት ጊዜያት የአፈር ማዳበሪያውን በማጓጓዝ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ለማድረስ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
የግብዓት አቅርቦትና ስርጭቱም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ የሚካሄድ በመሆኑ በፊት የነበሩትን አሰራር ችግሮች ከመቅረፍ ባለፈ አርሶ አደሩ ለእርሻ ልማት ስራው ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲያገኝ እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡
የዞኑ አርሶ አደሮች በአቅራቢያቸው በሚገኘው የማዳበሪያ ማሰራጫ ማዕከላት ተገኝተው በጊዜ መውሰድ እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026