
ታርጫ ፣የካቲት 5/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ጠየቁ።
የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በበኩላቸው የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለማከናወን በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ዛሬ በተጠናቀቀው የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄና አስተያየቶች አንስተው ምላሽ ተሰጥቷል።

ከምክር ቤቱ አባላትም የተለያዩ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና በሚመለከታቸው አስፈፃሚ አካላት ምላሽና ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።
በተለያዩ አካባቢዎች የተጀመሩ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ቀጣይ ትኩረት እንዲደረግ ከምክር ቤቱ አባላት ተነስቷል።
ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አቶ አማረ ብርሃኑ፤ ውጤታማ የሆኑ ጅምር የልማት ስራዎችና ሌሎችም ክልላዊ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀው የሁላችንም ድጋፍና ርብርብ ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል።
በተለይም በአንዳንድ አካባቢዎች ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንዲፋጠኑ የተበላሹትም እንዲጠገኑ ትኩረት ይሻል ብለዋል።
ሌላኛዋ የምክር ቤት አባል ወ/ሮ ከበቡሽ ከበደ፤ በተለይም በክረምት ወቅት ለህብረተሰቡ እንቅስቃሴ ችግር እየፈጠሩ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች በአፋጣኝ እልባት እንዲያገኙ ጠይቀዋል።
የመጠጥ ውሃና ሌሎችም በጅምር ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አስፈፃሚው አካል በልዩ ትኩረት እንዲሰራ የምክር ቤቱ አባላት አሳስበዋል።
የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀከቶች ግንባታ እንዲፋጠን በልዩ ትኩረት የሰራል ብለዋል።
የመጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማስፋት ሰፊ ጥረት መደረጉንና እየተደረገም መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የገጠር መንገድ ተደራሽነትን በተመለከተም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የግንባታና ጥገና ስራዎች መከናወናቸውን አንስተው በቀጣይም ብዙ ስራ ይጠብቀናል ብለዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ፋጂዮ ሳፒ፤ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥሉ ይሆናል ብለዋል።
ከፍተኛ በጀት የሚጠይቁ የድልድይና የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታም በሂደት የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026