የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በክልሉ በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በፍጥነት ሊጠናቀቁ ይገባል - የክልሉ ምክር ቤት አባላት</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

ታርጫ ፣የካቲት 5/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በግንባታ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የክልሉ ምክር ቤት አባላት ጠየቁ።

የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በበኩላቸው የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለማከናወን በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።

ዛሬ በተጠናቀቀው የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄና አስተያየቶች አንስተው ምላሽ ተሰጥቷል።


ከምክር ቤቱ አባላትም የተለያዩ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና በሚመለከታቸው አስፈፃሚ አካላት ምላሽና ማብራሪያ እየተሰጠ ነው።

በተለያዩ አካባቢዎች የተጀመሩ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ቀጣይ ትኩረት እንዲደረግ ከምክር ቤቱ አባላት ተነስቷል።

ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አቶ አማረ ብርሃኑ፤ ውጤታማ የሆኑ ጅምር የልማት ስራዎችና ሌሎችም ክልላዊ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀው የሁላችንም ድጋፍና ርብርብ ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል።

በተለይም በአንዳንድ አካባቢዎች ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንዲፋጠኑ የተበላሹትም እንዲጠገኑ ትኩረት ይሻል ብለዋል።

ሌላኛዋ የምክር ቤት አባል ወ/ሮ ከበቡሽ ከበደ፤ በተለይም በክረምት ወቅት ለህብረተሰቡ እንቅስቃሴ ችግር እየፈጠሩ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች በአፋጣኝ እልባት እንዲያገኙ ጠይቀዋል።

የመጠጥ ውሃና ሌሎችም በጅምር ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አስፈፃሚው አካል በልዩ ትኩረት እንዲሰራ የምክር ቤቱ አባላት አሳስበዋል።

የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፤ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀከቶች ግንባታ እንዲፋጠን በልዩ ትኩረት የሰራል ብለዋል።

የመጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማስፋት ሰፊ ጥረት መደረጉንና እየተደረገም መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የገጠር መንገድ ተደራሽነትን በተመለከተም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የግንባታና ጥገና ስራዎች መከናወናቸውን አንስተው በቀጣይም ብዙ ስራ ይጠብቀናል ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ፋጂዮ ሳፒ፤ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥሉ ይሆናል ብለዋል።

ከፍተኛ በጀት የሚጠይቁ የድልድይና የመንገድ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታም በሂደት የሚሰሩ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.