ደሴ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የተተገበረው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖችን ኑሮ በማሻሻልና የከተሞችን ገጽታ በመቀየር አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ገለጸ።
በፕሮግራሙ በኮምቦልቻ ከተማ በከተማ ግብርና የተሰሩ የተለያዩ የልማት ተግባራት ዛሬ በባለድርሻ አካላት ተጎብኝተዋል።
በዚህ ወቅት የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ እንዳመለከቱት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ ከ123 ሺህ የሚበልጡ ወገኖችን በፕሮግራሙ በማቀፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎችን በአካባቢ ልማት፣ ሥራ እድል ፈጠራና ማህበራዊ ተቋማት ግንባታ በማሳተፍ ኑሯቸው እንዲሻሻል የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ተናገረዋል።
በከተሞችም ተጠቃሚዎችን በጽዳትና ውበት፣ በጎርፍ መከላከል፣ በተፈጥሮ ሀብት ልማት፣ በመንገድ ሥራና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች በማሰማራት የከተሞች ገጽታ እንዲቀየር የሚያስችል ስራ ተሰርቷል ብለዋል።
የፕሮግራም ተጠቃሚዎችም በሰሩት ልክ ከሚከፈላቸው ክፍያ በመቆጠብና በተመቻቸላቸው ተጨማሪ ብድር በመታገዝ በልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ ዘርፎች በመሰማራት ጥሪት ማፍራታቸውን ገልጸዋል።
በዚህ ዓመት ጥሪት ያፈሩ ወገኖችን በማስመረቅ በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችል ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ እየተሰራ መሆኑንጠቁመዋል።
የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፕሮግራም ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ እታፈራሁ አሰግደው በበኩላቸው እንዳሉት፤ ተጠቃሚዎች ቀደም ሲል ጥቅም የማይሰጡና የቆሻሻ መጠያ የሆኑ ቦታዎችን በማልማት ላይ ይገኛሉ።
በተሰጣቸው ቦታ ላይም የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን በማልማት ከራሳቸው ፍጆታ አልፈው ለአካባቢው ገበያ በማቅረብ ገበያ ማረጋጋት ላይ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።
በኮምቦልቻ ከተማ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ከሆኑን ወስጥ አቶ አብዱራህማን አህመድ በሰጡት አስተያየት፤ መስራት የሚችል ጉልበት እያላቸው በገንዘብና በቦታ እጦት ተቸግረው እንደቆዩ አስታውሰዋል።
በፕሮግራሙ ከታቀፉ ወዲህ በተሰጣቸው የክህሎት ስልጠና በመጠቀም በከተማ ግብርና በመሰማራት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ጥሪት እያፈሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025