
አዲስ አበባ፣ የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በአዲስ አፍሪካ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን ዐውደ-ርዕይ ጎብኝተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ሚኒስትሮች፣ የ46ኛው የአፍሪካ ኀብረት መደበኛ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ተሳታፊ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች፣ አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶች ዐውደ-ርዕዩን ጎብኝተዋል።
በዐውደ-ርዕዩ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለብዝኅ ኢኮኖሚ ግንባታ በሰጠችው ትኩረት በግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን መስክ የተመዘገቡ ስኬቶች ለዕይታ ቀርበዋል።
በተጨማሪም በግሉ ዘርፍ ግዙፍ ኩባንያዎች የቡና፣ አልባሳት፣ የጌጣጌጥ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ውጤት አምራቾች አገልግሎቶቻቸውን አቅርበዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026