የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በሰሜን ወሎ ዞን በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሰባት ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

ወልድያ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- በሰሜን ወሎ ዞን በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሰባት ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የዞኑ እንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የሰሜን ወሎ ዞን የሌማት ቱሩፋት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በስታይሽ ከተማ ዛሬ ተካሂዷል።


የተጠሪ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ነጋ ጌታቸው፣ በውይይቱ ላይ እንዳሉት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በስራ እድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋትና የስራ ባህል በመቀየር አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

በዚህም በዞኑ የሚገኙ ሰባት ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችን በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ መደረጉን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ስጋ፣ እንቁላልና አትክልትና ፍራፍሬ ለገበያ በማቅረብ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በተጨማሪም በአሳ እርባታ የተሻሉ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው በዘርፉ ወጣቶችን በአሳ ልማት በማሰማራት አሁን ላይ ለገበያ የአሳ ምርት ማቅረብ መጀመራቸውን ሀላፊው ጠቅሰዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ንጋቱ፤ በዞኑ የሌማት ቱርፋት ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ አበረታች ለውጦች እየተገኙ ነው።


ዘርፉ ከምግብ አቅርቦት ባለፈ የስራ እድል በመፍጠር የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር በምግብ ራስን ለመቻልና ህብረተሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።

የዛሬው ውይይትም በዘርፉ አፈጻጸም ላይ የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መድረክ መሆኑን አስረድተዋል።

በውይይት መድረኩ ላይም የሰሜን ወሎ ዞን የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.