የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ኃይል ልማት ቀጣናውን ለማስተሳሰር በትኩረት እየሰራች ነው-ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ኃይል ልማት ምስራቅ አፍሪካን ለማስተሳሰር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ፡፡


ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ኃይል ልማት ምስራቅ አፍሪካን ለማስተሳሰር በትኩረት እየሰራች መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ፡፡


ስምንተኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም “ከእመርታ ወደ ብልጽግና፤ የአፍሪካን ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች አቅም ማጠናከር” በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ የኢኮኖሚክ ኮሚሽን ተካሂዷል፡፡


የቢዝነስ ፎረሙ በአፍሪካ የቁም እንስሳት፣ግብርና እና ፋርማሲዩቲካል ዘርፎች ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለት እና ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ልማት ላይ ያተኮረ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡


በፎረሙ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፤ የአየር ንብረት ለውጥን እና አደጋን መቋቋም የሚችል መሰረት ልማት ማስፋፋት ለዘርፉ መነቃቃት ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም አንስተዋል።


ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያካሄደችው አብዮት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ መሆን የሚችል መሆኑን አንስተው፥ በቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍም ጠንካራ ሥራዎችን በመስራት ላይ እንደምትገኝ ጠቁመዋል፡፡


በአፍሪካ የማምረት አቅምን በማሳደግ ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ላይ ትኩረት ሊደረጉ እንደሚገባም ጠቁመዋል።


ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ኢንቨስተሮችን በመሳብ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፥ በጨርቃጨርቅ ዘርፍ አመርቂ ስራዎች መስራቷንም ገልጸዋል፡፡


በቅርቡ ያካሄደችው የኢኮኖሚ ሪፎርም የኢንቨስትመንት ፍላጎት እንዲጨምር በማድረግ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ መነቃቃትን እንደፈጠረም ነው የጠቆሙት።


ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት ምስራቅ አፍሪካን ለማስተሳሰር እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል፡፡


ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ቀጣናውን ለማስተሳሰር ጥረት እያደረገች ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የታላቁ ህዳሴና የኮይሻ የታዳሽ ኤሌክትሪክ ማምንጫ ግድቦች ለዚህ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


የአፍሪካን አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማሳደግ ለፈጠራ እንዲሁም ለስራና ክህሎት ትምህርት ትኩረት መስጠት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡


በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሥራ አስፈፃሚ ክላቨር ጌቴቴ በበኩላቸው፥ በአህጉሪቱ እሴትን በመጨመር የሚሰሩ ስራዎንችን ማሳደግ የወጣቶችን የስራ ዕድል ፈጠራ ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


በአህጉሪቱ የመድኃኒት ምርት አቅርቦትን በማሳደግ እንዲሁም በሌሎችም የማምረት አቅምን በማጠናከር ለኢኮኖሚው መረጋጋትና ዕድገት መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡


የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀ-መንበር ሞኒክ ንሳንዛባጋንዋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳን ለማሳካት አለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ የእሴት ሰንሰለቶችን በሚያጎለብቱ ዕቅዶች ዙሪያ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናዎች መጠናከር እንዳላባቸው የጠቆሙት ምክትል ሊቀመንበሯ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለኢንዱስትራላይዜሽን መስፋፋት ብሎም ለእሴት ሰንሰለት መጨመር ትልቅ ሚና ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡


ፎረሙን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ከአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን እና ከአረብ ባንክ ፎር ኢኮኖሚክ ዴቨሎፕመንት ጋር በመተባበር እንዳዘጋጁት ተገልጿል።


የአፍሪካ የቢዝነስ ፎረም እ.አ.አ ከ2018 ጀምሮ በየዓመቱ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.