የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በክልሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የማድረግ ስራዎች ተጀምረዋል</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።

የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ቦኮና ጉታ እንደተናገሩት፥ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው።

ከተጀመሩ ጥረቶች መካከል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል ብለዋል።

በዚህ ዓመትም በክልሉ በአስር ሆስፒታሎችና በአምስት ጤና ጣቢያዎች ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ተግባራዊ ተደርጓል ነው ያሉት።

በቀጣይም በክልሉ በሁሉም የጤና ተቋማት ከወረቀት ነጻ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠት ከተጀመረባቸው ተቋማት መካከል የመቱ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ካርል ሆስፒታል አንዱ ነው።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሶላን በቀለ፤ በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ እየተሰጠ የሚገኘው የሕክምና አገልግሎት ከወረቀት ነጻ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ለተገልጋዩ የተቀላጠፈ የሕክምና አገልግሎት መስጠት እያስቻለ ሲሆን ከዚህ በፊት ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎችም መቀነሳቸውን ተናግረዋል።

የመቱ ሆስፒታል ከወረቀት ነጻ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን በጤና ሚኒስቴር አመራሮችና በክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮች ተጎብኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.