
መቱ፤ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።
የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ቦኮና ጉታ እንደተናገሩት፥ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው።
ከተጀመሩ ጥረቶች መካከል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል ብለዋል።
በዚህ ዓመትም በክልሉ በአስር ሆስፒታሎችና በአምስት ጤና ጣቢያዎች ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ተግባራዊ ተደርጓል ነው ያሉት።
በቀጣይም በክልሉ በሁሉም የጤና ተቋማት ከወረቀት ነጻ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠት ከተጀመረባቸው ተቋማት መካከል የመቱ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ካርል ሆስፒታል አንዱ ነው።
የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሶላን በቀለ፤ በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ እየተሰጠ የሚገኘው የሕክምና አገልግሎት ከወረቀት ነጻ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ለተገልጋዩ የተቀላጠፈ የሕክምና አገልግሎት መስጠት እያስቻለ ሲሆን ከዚህ በፊት ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎችም መቀነሳቸውን ተናግረዋል።
የመቱ ሆስፒታል ከወረቀት ነጻ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን በጤና ሚኒስቴር አመራሮችና በክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮች ተጎብኝቷል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026