የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የኢትዮጵያ ልዑክ በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈ ነው</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።


ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ Commit to life በሚል መሪ ቃል በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካንን በመምራት እየተሳተፍን እንገኛለን ብለዋል።

ኮንፍረንሱ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚቆይም አስታውቀዋል።

ይህ ኮንፍረንስ በአለም ሀገራት በመንገድ ደህንነት ዙሪያ ያሉ ቁልፍ ተግዳሮቶችን ለመፍታትና የትራፊክ አደጋዎችንና ጉዳቶችን ለመቀነስ የሚያስችሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንዲሁም ቃልኪዳኖችን ይበልጥ ለማጠናከር ያግዛል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.