
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ Commit to life በሚል መሪ ቃል በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካንን በመምራት እየተሳተፍን እንገኛለን ብለዋል።
ኮንፍረንሱ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚቆይም አስታውቀዋል።
ይህ ኮንፍረንስ በአለም ሀገራት በመንገድ ደህንነት ዙሪያ ያሉ ቁልፍ ተግዳሮቶችን ለመፍታትና የትራፊክ አደጋዎችንና ጉዳቶችን ለመቀነስ የሚያስችሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንዲሁም ቃልኪዳኖችን ይበልጥ ለማጠናከር ያግዛል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026