አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ Commit to life በሚል መሪ ቃል በሞሮኮ ማራካሽ በተጀመረው 4ኛው የአለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት የሚኒስትሮች ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካንን በመምራት እየተሳተፍን እንገኛለን ብለዋል።
ኮንፍረንሱ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚቆይም አስታውቀዋል።
ይህ ኮንፍረንስ በአለም ሀገራት በመንገድ ደህንነት ዙሪያ ያሉ ቁልፍ ተግዳሮቶችን ለመፍታትና የትራፊክ አደጋዎችንና ጉዳቶችን ለመቀነስ የሚያስችሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንዲሁም ቃልኪዳኖችን ይበልጥ ለማጠናከር ያግዛል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025