
ደሴ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፡- ምርት በመደበቅ፣ ዋጋ በመጨመርና በሌሎችም ህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ አካላትን በመለየት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደሴ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
በደሴ ከተማ ህገ ወጥ ንግድ ሲያከናውኑ የተገኙ 82 የንግድ ድርጅቶች እንዲታሸጉ መደረጉን የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል።
በዘርፉ ጎላ ያለ ህገ ወጥ ተግባር ፈጽመዋል የተባሉ 13 ግለሰቦችም ጉዳያቸው በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ በሂደት ላይ መሆኑንም ተገልጿል፡፡

የደሴ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሽመልስ ጌታቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ ገበያውን ለማረጋጋት በትኩረት እየሰራ ባለበት ወቅት የኑሮ ውድነት እንዲከሰት የሚሰሩ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን አንታገስም ብለዋል፡፡
በዚህም ምርት በመደበቅ፣ ዋጋ በመጨመርና በሌሎችም ህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩትን በመለየት እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡
ህገወጦችን ሥርዓት ለማስያዝ እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በመደገፍ ህብረተሰቡ እያደረገ ያለው ትብበር ማጠናከር እንዳለበትም አመልክተዋል።
በቂ ምርት ከተለያየ አካባቢ ወደ ከተማው እየገባ መሆኑንም ምክትል ከንቲባው አረጋግጠዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮናስ እንዳለ በበኩላቸው፤ በቅንጅት በተደረገ ክትትልና ቁጥጥር ያለ ምክንያት በምርት ላይ ዋጋ የጨመሩ፣ ምርት የደበቁ፣ ያለ ንግድ ፍቃድ ሲሰሩ የተገኙ 82 የንግድ ድርጅቶች ታሽገዋል ብለዋል፡፡
በተደረገ ክትትል እና ቁጥጥር በአምስት ሊትር ዘይት ላይ የ400 ብር እና በአንድ ኩንታል ስንዴ ዱቄት ላይ የ1ሺህ 600 ብር ጭማሪ የተደረገባቸው ምርቶችን መገኘታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።
ተከማችቶ የተገኘው ምርትም በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዘርፉ ጎላ ያለ ህገ ወጥ ተግባር ፈጽመዋል የተባሉ 13 ግለሰቦችም ጉዳያቸው በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ በሂደት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በደሴ ከተማ አስተዳደር ለገበያ ማረጋጊያ ከተመደበው ገንዘብ በ20 ሚሊዮን ብሩ የተለያየ ምርት ተገዝቶ ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑም ታውቋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026