የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወልዲያ ከተማ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ጎበኙ</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ የካቲት 12/2017( ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬና የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወልዲያ ከተማ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

በወልዲያ ከተማ ከተጎበኙት የልማት ስራዎች መካከል 30 ሜትር ስፋት ያለው ዘጠኝ ኪሎ ሜትር የቀለበት መንገድ፣ የገበያ ማዕከልና ዲጂታል የሕዝብ ቤተ- መጻሕፍትና ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል።

የቀለበት መንገዱ በከተማ አስተዳደሩ 750 ሚሊዮን ብር በጀት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተመላክቷል።

በተመሳሳይም በከተማዋ በ16 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው ቤተ-መጻሕፍትም በስራ ኃላፊዎቹ ተጎብኝቷል።

የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ሰሞኑን በሰሜን ወሎ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.