
ወልዲያ፤ የካቲት 12/2017( ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬና የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወልዲያ ከተማ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
በወልዲያ ከተማ ከተጎበኙት የልማት ስራዎች መካከል 30 ሜትር ስፋት ያለው ዘጠኝ ኪሎ ሜትር የቀለበት መንገድ፣ የገበያ ማዕከልና ዲጂታል የሕዝብ ቤተ- መጻሕፍትና ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል።
የቀለበት መንገዱ በከተማ አስተዳደሩ 750 ሚሊዮን ብር በጀት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
በተመሳሳይም በከተማዋ በ16 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው ቤተ-መጻሕፍትም በስራ ኃላፊዎቹ ተጎብኝቷል።
የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ሰሞኑን በሰሜን ወሎ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸው ይታወሳል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026