
ወልዲያ፤ የካቲት 12/2017( ኢዜአ)፡-የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬና የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወልዲያ ከተማ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
በወልዲያ ከተማ ከተጎበኙት የልማት ስራዎች መካከል 30 ሜትር ስፋት ያለው ዘጠኝ ኪሎ ሜትር የቀለበት መንገድ፣ የገበያ ማዕከልና ዲጂታል የሕዝብ ቤተ- መጻሕፍትና ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል።
የቀለበት መንገዱ በከተማ አስተዳደሩ 750 ሚሊዮን ብር በጀት እየተከናወነ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
በተመሳሳይም በከተማዋ በ16 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ ያለው ቤተ-መጻሕፍትም በስራ ኃላፊዎቹ ተጎብኝቷል።
የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ሰሞኑን በሰሜን ወሎ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸው ይታወሳል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026