አዲስ አበባ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦በኢፌዴሪ አየር ኃይል ውስጥ የተሰራችው ፀሃይ - 2 የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወን መቻሏን የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአቪየሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ኮሎኔል መሰረት ጌታቸው ገልፀዋል።
ፀሃይ -2 አውሮፕላን ለበረራ ማሰልጠኛና ለሌሎች አገልግሎት መዋል የምትችል መሆኑን ያስታወቁት ኮሎኔል መሰረት ጌታቸው የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት መፈፀም የሚያስችላትን የዘመኑን የአቭዬሽን ቴክኖሎጂ መታጠቋንም አብራርተዋል።
የአውሮፕላኗ ስኬታማ የሙከራ በረራ አየር ኃይሉ የደረሰበትን የከፍታ ጉዞ ጠቋሚ ነው ያሉት ምክትል አዛዡ በቀጣይነትም ወደ ምርት ሂደት ለመሸጋገር ፋብሪካውን የማደራጀት ፣የመፈተሻ እቃዎችን የማሟላትና የሙያተኞችን አቅም የማጎልበት ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
የትራንስፖርት አውሮፕላን ስኳድሮን አዛዥ እና አብራሪ እንዲሁም የፀሃይ -2 የሙከራ በረራን በስኬት ያካሄዱት ሻለቃ ፍቃዱ ደምሴ በበኩላቸው አውሮፕላኗ አለም የደረሰበትን የአውሮፕላን ቴክኖሎጂ የታጠቀች የበረራ አቅሟም አስተማማኝ እና ተቋሙ ለያዘው የወደፊት ራዕይ ጉልህ አስተዋፅዖ የምታበረክት መሆኗን ገልፀዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025