የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ለግብርና ግብአት የመጋዘንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲሰጥ በአክሱም ከተማ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ተመረቀ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አክሱም፤የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡-ለግብርና ግብአት የመጋዘንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲሰጥ በአክሱም ከተማ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ተመረቀ።

በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን በ70 ሚሊዮን ብር የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ለግብርና ግብአትና ለመሳሪያዎች መጋዘንና ሌሎችም አገልግሎቶች የሚውል መሆኑ ታውቋል።

በህንፃው ምረቃ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ክፍሌ ወልደማሪያም፤ የተገነባው ባለ ሶስት ወለል ህንጻ ለግብርና ስራ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

ህንፃው የግብርና መሳሪያዎችና የግብአት መጋዘን ያለው በመሆኑ ግብአቶችን ለአርሶ አደሮች በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስለመሆኑ አንስተዋል።

መጋዘኑ በአንድ ጊዜ ከ60 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያና ሌሎችንም የግብርና ግብአቶች መያዝ የሚችል መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለይም ለአክሱምና አድዋ፡ ሽሬና አካባቢው ለሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ግብአቶችን በቅርበትና በአፋጣኝ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ምክትል ከንቲባ አበበ ብርሃነ፤ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ በተለይም ለአርሶ አደሮች አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ በከተማው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ሲሉም አረጋግጠዋል።

ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በፊት በውቅሮ ማራይ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገንብቶና የውስጥ ቁሳቁሶችንም አሟልቶ ማስረከቡ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.