
አክሱም፤የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡-ለግብርና ግብአት የመጋዘንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲሰጥ በአክሱም ከተማ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ተመረቀ።
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን በ70 ሚሊዮን ብር የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ለግብርና ግብአትና ለመሳሪያዎች መጋዘንና ሌሎችም አገልግሎቶች የሚውል መሆኑ ታውቋል።
በህንፃው ምረቃ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ክፍሌ ወልደማሪያም፤ የተገነባው ባለ ሶስት ወለል ህንጻ ለግብርና ስራ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
ህንፃው የግብርና መሳሪያዎችና የግብአት መጋዘን ያለው በመሆኑ ግብአቶችን ለአርሶ አደሮች በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስለመሆኑ አንስተዋል።
መጋዘኑ በአንድ ጊዜ ከ60 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያና ሌሎችንም የግብርና ግብአቶች መያዝ የሚችል መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይም ለአክሱምና አድዋ፡ ሽሬና አካባቢው ለሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ግብአቶችን በቅርበትና በአፋጣኝ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል።
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ምክትል ከንቲባ አበበ ብርሃነ፤ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ በተለይም ለአርሶ አደሮች አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል።
ኮርፖሬሽኑ በከተማው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ሲሉም አረጋግጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በፊት በውቅሮ ማራይ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገንብቶና የውስጥ ቁሳቁሶችንም አሟልቶ ማስረከቡ ይታወሳል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026