
አክሱም፤የካቲት 13/2017 (ኢዜአ) ፡-ለግብርና ግብአት የመጋዘንና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲሰጥ በአክሱም ከተማ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ተመረቀ።
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን በ70 ሚሊዮን ብር የተገነባው ሁለገብ ህንፃ ለግብርና ግብአትና ለመሳሪያዎች መጋዘንና ሌሎችም አገልግሎቶች የሚውል መሆኑ ታውቋል።
በህንፃው ምረቃ ስነ ስርአት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ክፍሌ ወልደማሪያም፤ የተገነባው ባለ ሶስት ወለል ህንጻ ለግብርና ስራ የላቀ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
ህንፃው የግብርና መሳሪያዎችና የግብአት መጋዘን ያለው በመሆኑ ግብአቶችን ለአርሶ አደሮች በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ስለመሆኑ አንስተዋል።
መጋዘኑ በአንድ ጊዜ ከ60 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያና ሌሎችንም የግብርና ግብአቶች መያዝ የሚችል መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይም ለአክሱምና አድዋ፡ ሽሬና አካባቢው ለሚገኙ አርሶ አደሮች የግብርና ግብአቶችን በቅርበትና በአፋጣኝ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ገልጸዋል።
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአክሱም ከተማ ምክትል ከንቲባ አበበ ብርሃነ፤ የተገነባው ሁለገብ ህንፃ በተለይም ለአርሶ አደሮች አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል።
ኮርፖሬሽኑ በከተማው ለሚያከናውናቸው ስራዎች ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ሲሉም አረጋግጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ ከዚህ በፊት በውቅሮ ማራይ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገንብቶና የውስጥ ቁሳቁሶችንም አሟልቶ ማስረከቡ ይታወሳል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026