የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በጎንደር ከተማ በፌዴራል መንግስት እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የሠላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እና ሌሎችም የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።


በጉብኝታቸውም የጎንደር ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ዳግም ግንባታው በመፋጠን ላይ የሚገኘውን የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግድብ የስራ እንቅስቃሴ ምልከታ አድርገዋል።


በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃውን የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ድባብን እንዲሁም አለም አቀፍ ቅርስ የሆነውን የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.