
ጎንደር፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በጎንደር ከተማ በፌዴራል መንግስት እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የሠላም ሚኒስትሩ መሀመድ እድሪስ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እና ሌሎችም የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የጎንደር ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት እንዲፈታ ዳግም ግንባታው በመፋጠን ላይ የሚገኘውን የመገጭ የመስኖና የመጠጥ ውሃ ግድብ የስራ እንቅስቃሴ ምልከታ አድርገዋል።

በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃውን የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ድባብን እንዲሁም አለም አቀፍ ቅርስ የሆነውን የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ስራንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026