የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ከሸገር ከተማ አስተዳደር፣ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።

ስምምነቱን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እንዲሁም የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ ፈርመዋል።


የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ አካዳሚው በዛሬው እለት ከሶስት ተቋማት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችሉትን ስምምነቶች መፈራረሙን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የእድገት ግስጋሴ እውን እንዲሆን የዘመኑ ከተሞችን መገንባትና ማልማት እንዲሁም ከተሞችን የሚመሩ አመራሮችን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

ለዚህም አካዳሚው የሸገር ከተማ አስተዳደር አመራሮችን አቅም ለማጎልበት እና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚሰራም ጠቁመዋል።


በተመሳሳይ ወጣቶችን በአመራርነት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።

የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) የከተማዋን እድገት በማፋጠን ተወዳዳሪ ብሎም ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ እና የዘመነ አገልግሎትን መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ነገር ግን ከተማዋን ለማዘመን በተወሰነ አካል ብቻ በሚሰራ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አዳጋች መሆኑን ገልጸው ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት ይጠይቃል ብለዋል።

በተለይም አንድን ከተማ እውቀትን በአግባቡ በመጠቀም ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም በጥናትና ምርምር እንዲሁም በስልጠና ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ይህን መነሻ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የአቅም ግንባታና ሌሎች ለከተማው የሚጠቅሙ ስራዎችን ከአካዳሚው ጋር ለመስራት ስምምነቱ መፈረሙን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ በበኩላቸው የወጣቶችን የአመራርነት አቅም ለመገንባትና ሌሎች ከወጣቶች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ስምምነቱ ትልቅ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.