
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ከሸገር ከተማ አስተዳደር፣ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።
ስምምነቱን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እንዲሁም የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ ፈርመዋል።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ አካዳሚው በዛሬው እለት ከሶስት ተቋማት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችሉትን ስምምነቶች መፈራረሙን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የእድገት ግስጋሴ እውን እንዲሆን የዘመኑ ከተሞችን መገንባትና ማልማት እንዲሁም ከተሞችን የሚመሩ አመራሮችን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ለዚህም አካዳሚው የሸገር ከተማ አስተዳደር አመራሮችን አቅም ለማጎልበት እና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

በተመሳሳይ ወጣቶችን በአመራርነት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።
የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) የከተማዋን እድገት በማፋጠን ተወዳዳሪ ብሎም ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ እና የዘመነ አገልግሎትን መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
ነገር ግን ከተማዋን ለማዘመን በተወሰነ አካል ብቻ በሚሰራ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አዳጋች መሆኑን ገልጸው ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት ይጠይቃል ብለዋል።
በተለይም አንድን ከተማ እውቀትን በአግባቡ በመጠቀም ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም በጥናትና ምርምር እንዲሁም በስልጠና ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ይህን መነሻ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የአቅም ግንባታና ሌሎች ለከተማው የሚጠቅሙ ስራዎችን ከአካዳሚው ጋር ለመስራት ስምምነቱ መፈረሙን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ በበኩላቸው የወጣቶችን የአመራርነት አቅም ለመገንባትና ሌሎች ከወጣቶች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ስምምነቱ ትልቅ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026