ወላይታ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 524 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እንደ ሀገር ብልጽግናን ለማረጋገጥና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎችን ለማጠናከር በየመስኩ ብቁ የሰለጠነ የሰው ሀይል ያስፈልጋል።
በመሆኑም ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ ምርምር በማድረግና በአዳዲስ እሳቤዎች የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
በተለይ የአርሶ አደሩን ባህላዊ የአመራረት ዘይቤ በመቀየር ውጤታማ ለማድረግ በቅርበት ሆነው መስራት እንዳለባቸውም አመልክትዋል።
ሀገር ወደ ተሻለ ደረጃ እንድትደርስ የመቻቻል፣ የመደጋገፍና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበትና ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር የበኩላቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መስኮች በዕውቀትና በክህሎት የሰለጠነ የሰው ሀይል እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ምርምሮች እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን ማከናወኑንም ገልጸዋል።
የዛሬ ተመራቂዎችም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው በቀጣይ ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል።
በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቁት ተገኝ ሀይሉ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ባገኙት እውቀት ሀገርና ህዝብን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከዛሬ ምሩቃን መካከል 737ቱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በወላይታ ሶዶና ታርጫ ካምፓሶች በመደበኛ፣ በማታ፣ በእረፍት ቀናትና በርቀት የትምህርት መርሀግብሮች 39 ሺህ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025