
ወላይታ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 524 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እንደ ሀገር ብልጽግናን ለማረጋገጥና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎችን ለማጠናከር በየመስኩ ብቁ የሰለጠነ የሰው ሀይል ያስፈልጋል።
በመሆኑም ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ ምርምር በማድረግና በአዳዲስ እሳቤዎች የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
በተለይ የአርሶ አደሩን ባህላዊ የአመራረት ዘይቤ በመቀየር ውጤታማ ለማድረግ በቅርበት ሆነው መስራት እንዳለባቸውም አመልክትዋል።
ሀገር ወደ ተሻለ ደረጃ እንድትደርስ የመቻቻል፣ የመደጋገፍና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበትና ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር የበኩላቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መስኮች በዕውቀትና በክህሎት የሰለጠነ የሰው ሀይል እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ምርምሮች እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን ማከናወኑንም ገልጸዋል።
የዛሬ ተመራቂዎችም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው በቀጣይ ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል።
በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቁት ተገኝ ሀይሉ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ባገኙት እውቀት ሀገርና ህዝብን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከዛሬ ምሩቃን መካከል 737ቱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በወላይታ ሶዶና ታርጫ ካምፓሶች በመደበኛ፣ በማታ፣ በእረፍት ቀናትና በርቀት የትምህርት መርሀግብሮች 39 ሺህ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026