
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15ቀን 2017(ኢዜአ) አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በደብረብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና በፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።
የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ ዋን ወይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ፋብሪካንና ጅንሹ ኢትዮጵያ የቴክስታይል ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
አቶ አብርሃም ማርሻሎ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ስራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።
በተለይም በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ የአካባቢውን የቱሪዝም ልማት ለማሳደግና ለስራ እድል ፈጠራ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
የደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፥ በከተማዋ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የንግድና የኢንቨስትመንት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ባለፉት ሰባት ወራት 17 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፥ የተካሄደው ጉብኝትም ከከፍተኛ አመራሮች በሚገኝ ግብዓት በቀጣይ የላቀ ልማት ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026