የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15ቀን 2017(ኢዜአ) አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በደብረብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና በፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።


የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ ዋን ወይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ፋብሪካንና ጅንሹ ኢትዮጵያ የቴክስታይል ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።


አቶ አብርሃም ማርሻሎ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ስራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።


በተለይም በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ የአካባቢውን የቱሪዝም ልማት ለማሳደግና ለስራ እድል ፈጠራ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ብለዋል።


የደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፥ በከተማዋ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የንግድና የኢንቨስትመንት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ባለፉት ሰባት ወራት 17 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፥ የተካሄደው ጉብኝትም ከከፍተኛ አመራሮች በሚገኝ ግብዓት በቀጣይ የላቀ ልማት ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026