የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ዩኒየኑ ለበልግ የምርት ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦ የሲኮ መንዶ የአርሶ አደሮች ህብረት ሥራ ዩኒየን ለ2017/18 የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን ገለጸ።

የዩኒየኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ታዬ እንደገለጹት፥ ዩኒየኑ ለዘንድሮው የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው።

ዩኒየኑ በእስካሁኑ ሂደት ካቀረበው ከ100 ሺህ በላይ የአፈር ማዳበሪያ 50 በመቶ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አመልክቷል።

በተለይም ዩኒየኑ ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ችግር በመቅረፍ በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች የተሻለ የሥርጭት ሂደት መመዝገቡን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውን ወደ ዞኑ የማጓጓዝ ስራው በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን በየቀኑ 25 መኪና የአፈር ማዳበሪያ ወደ ዩኒየኑ መጋዘን እንደሚገባም አረጋግጠዋል።


ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ከ100 ሺህ ሊትር የሚበልጡ የተለያዩ አይነት ኬሚካሎችን ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዞኑ የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ ደበሌ ሀቤቤ በበኩላቸው፥ በዞኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል።

በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የሚከናወኑ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ 3 ዩኒየኖችና 34 የህብረት ሥራ ማህበራት በማዳበሪያና ሌሎች የግብርና ግብዓቶች ስርጭት ላይ እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.