
ሮቤ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦ የሲኮ መንዶ የአርሶ አደሮች ህብረት ሥራ ዩኒየን ለ2017/18 የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን ገለጸ።
የዩኒየኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ታዬ እንደገለጹት፥ ዩኒየኑ ለዘንድሮው የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው።
ዩኒየኑ በእስካሁኑ ሂደት ካቀረበው ከ100 ሺህ በላይ የአፈር ማዳበሪያ 50 በመቶ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አመልክቷል።
በተለይም ዩኒየኑ ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ችግር በመቅረፍ በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች የተሻለ የሥርጭት ሂደት መመዝገቡን ተናግረዋል።
የአፈር ማዳበሪያውን ወደ ዞኑ የማጓጓዝ ስራው በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን በየቀኑ 25 መኪና የአፈር ማዳበሪያ ወደ ዩኒየኑ መጋዘን እንደሚገባም አረጋግጠዋል።

ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ከ100 ሺህ ሊትር የሚበልጡ የተለያዩ አይነት ኬሚካሎችን ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የዞኑ የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ ደበሌ ሀቤቤ በበኩላቸው፥ በዞኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል።
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የሚከናወኑ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ 3 ዩኒየኖችና 34 የህብረት ሥራ ማህበራት በማዳበሪያና ሌሎች የግብርና ግብዓቶች ስርጭት ላይ እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026