የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የፌዴራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ስራ ጎበኙ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፡-የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ።

ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ የጎበኙት በከተማው ከድሮው ጊዮን ሆቴል እስከ አጅፕ በመጀመሪያ ምዕራፍ የተገነባውን የኮሪደር ልማት ነው።

የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ በከተማው 22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለመስራት ታቅዶ የመጀመሪያው ምዕራፍ 3 ኪሎ ሜትር እየተጠናቀቀ መሆኑ ተናግረዋል።

የስራ ኃላፊዎቹ ከኮሪደር ልማት ስራው በተጨማሪም በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ ሌሎች የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተሞችና መሰሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)፤ የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.