
ባህር ዳር፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፡-የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ።
ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ የጎበኙት በከተማው ከድሮው ጊዮን ሆቴል እስከ አጅፕ በመጀመሪያ ምዕራፍ የተገነባውን የኮሪደር ልማት ነው።
የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ በከተማው 22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለመስራት ታቅዶ የመጀመሪያው ምዕራፍ 3 ኪሎ ሜትር እየተጠናቀቀ መሆኑ ተናግረዋል።
የስራ ኃላፊዎቹ ከኮሪደር ልማት ስራው በተጨማሪም በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ ሌሎች የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተሞችና መሰሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)፤ የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026