
ባህር ዳር፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፡-የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ።
ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ የጎበኙት በከተማው ከድሮው ጊዮን ሆቴል እስከ አጅፕ በመጀመሪያ ምዕራፍ የተገነባውን የኮሪደር ልማት ነው።
የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ በከተማው 22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለመስራት ታቅዶ የመጀመሪያው ምዕራፍ 3 ኪሎ ሜትር እየተጠናቀቀ መሆኑ ተናግረዋል።
የስራ ኃላፊዎቹ ከኮሪደር ልማት ስራው በተጨማሪም በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ ሌሎች የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተሞችና መሰሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)፤ የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026