አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማኀበር ወይዘሮ በረከት ወርቁን የማህበሩ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ።
የማኀበሩ ምስረታና ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ የተካሄደ ሲሆን ጉባዔው የማህበሩን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫና የመተዳደሪያ ደንብ ተወያይቶ አጽድቋል።
በዚህም ማህበሩ ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ከቀረቡ 12 ዕጩዎች መካከል በተለምዶ 'በረከት ገበሬዋ' በሚል ስም የሚታወቁት ወይዘሮ በረከት ወርቁን በፕሬዝዳንትነት መርጧል።
ጉባዔው ሳራ ሀሰንን ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ትልቅሰው ገዳሙን ደግሞ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።
በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ መስከረም ባሕሩ የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ ማህበሩ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025