
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማኀበር ወይዘሮ በረከት ወርቁን የማህበሩ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ።
የማኀበሩ ምስረታና ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ የተካሄደ ሲሆን ጉባዔው የማህበሩን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫና የመተዳደሪያ ደንብ ተወያይቶ አጽድቋል።

በዚህም ማህበሩ ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ከቀረቡ 12 ዕጩዎች መካከል በተለምዶ 'በረከት ገበሬዋ' በሚል ስም የሚታወቁት ወይዘሮ በረከት ወርቁን በፕሬዝዳንትነት መርጧል።
ጉባዔው ሳራ ሀሰንን ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ትልቅሰው ገዳሙን ደግሞ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።
በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ መስከረም ባሕሩ የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ ማህበሩ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026