የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ወይዘሮ በረከት ወርቁ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማኀበር ፕሬዚዳንት ሆኑ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማኀበር ወይዘሮ በረከት ወርቁን የማህበሩ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ።

የማኀበሩ ምስረታና ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ የተካሄደ ሲሆን ጉባዔው የማህበሩን ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫና የመተዳደሪያ ደንብ ተወያይቶ አጽድቋል።


በዚህም ማህበሩ ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ከቀረቡ 12 ዕጩዎች መካከል በተለምዶ 'በረከት ገበሬዋ' በሚል ስም የሚታወቁት ወይዘሮ በረከት ወርቁን በፕሬዝዳንትነት መርጧል።

ጉባዔው ሳራ ሀሰንን ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ትልቅሰው ገዳሙን ደግሞ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ መስከረም ባሕሩ የምርጫ ሂደቱ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይ ማህበሩ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.