
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስገነዘቡ።
ሚኒስቴሩ የኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩትን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት አፈፃፀም ገምግሟል፡፡
በዚህ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት፣ ኢንስቲትዩቱ ምሳሌ የሚሆን አካታችነትንና በብዙ እጥፍ ያደገ ተደራሽነትን አሳይቷል፡፡

በተለይም በክህሎት ልማትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃትን በመፍጠር የሚታዩ ውጤቶችን ማስመዝገብ ችሏል ብለዋል፡፡
በቀጣይ የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባው ሚኒስትሯ መጠቆማቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
በክህሎት ልማቱ ላይ ያለውን የአሰለጣጠን ዘይቤ ፈጠራ የታከለበት እንዲሆን ማድረግ እና የኢንተርፕራይዝ ምስረታ ከልማዳዊ አሠራሮች የተላቀቀና ክፍተቶችን የሚሞላ አድርጎ መቃኘት ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ ማስቀመጣቸውም በመረጃው ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀምም ተገምግሟል፡፡
ኢንስቲትዩቱ የጀመራቸው የሪፎርም ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል፡፡
በቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦትና ፍላጎት ያለመጣጣም በመኖሩ ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበና የበይነ መረብ የሥልጠና አማራጮችንም ጭምር የሚጠቀም የሰው ኃይል ልማት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በዘርፉ በልምድ የተገኘ ሙያን ቴክኒካዊና ባህሪያዊ ብቃቶችን መዝኖ እውቅና መስጠት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል።
ከእንግሊዘኛ በተጨማሪ በሌሎች የውጭ ቋንቋዎች ሥልጠና ላይ የተጀመሩ ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት፡፡
የባህል ምግቦችን በጥናት ለይቶ ወደ ሆቴሎች ሜኑ ለማስገባት የተጀመሩ ሥራዎች ባህሉን ከመጠበቅ ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና አካባቢያዊ ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026