የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ኢንስቲትዩቱ የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባዋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስገነዘቡ።

ሚኒስቴሩ የኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩትን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት አፈፃፀም ገምግሟል፡፡

በዚህ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት፣ ኢንስቲትዩቱ ምሳሌ የሚሆን አካታችነትንና በብዙ እጥፍ ያደገ ተደራሽነትን አሳይቷል፡፡


በተለይም በክህሎት ልማትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃትን በመፍጠር የሚታዩ ውጤቶችን ማስመዝገብ ችሏል ብለዋል፡፡

በቀጣይ የኢንተርፕርነርሺፕ ስነ-ምህዳር ግንባታ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባው ሚኒስትሯ መጠቆማቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

በክህሎት ልማቱ ላይ ያለውን የአሰለጣጠን ዘይቤ ፈጠራ የታከለበት እንዲሆን ማድረግ እና የኢንተርፕራይዝ ምስረታ ከልማዳዊ አሠራሮች የተላቀቀና ክፍተቶችን የሚሞላ አድርጎ መቃኘት ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ ማስቀመጣቸውም በመረጃው ተጠቁሟል፡፡


በተጨማሪም የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀምም ተገምግሟል፡፡

ኢንስቲትዩቱ የጀመራቸው የሪፎርም ተግባራት ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገልጸዋል፡፡

በቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦትና ፍላጎት ያለመጣጣም በመኖሩ ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበና የበይነ መረብ የሥልጠና አማራጮችንም ጭምር የሚጠቀም የሰው ኃይል ልማት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በዘርፉ በልምድ የተገኘ ሙያን ቴክኒካዊና ባህሪያዊ ብቃቶችን መዝኖ እውቅና መስጠት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

ከእንግሊዘኛ በተጨማሪ በሌሎች የውጭ ቋንቋዎች ሥልጠና ላይ የተጀመሩ ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል ነው ያሉት፡፡

የባህል ምግቦችን በጥናት ለይቶ ወደ ሆቴሎች ሜኑ ለማስገባት የተጀመሩ ሥራዎች ባህሉን ከመጠበቅ ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና አካባቢያዊ ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ከፍተኛ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አመላክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026