
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ ስምምነቱ ገቢራዊነት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።
ለሁለት ቀናት በጅቡቲ የተካሄደው የኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን ምስረታ የሚኒስትሮች መድረክ የጅቡቲ-ኢትዮጵያ-ደቡብ ሱዳን-ዩጋንዳ (DESSU) ኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ታሪካዊው ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ እና ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ንግድ፣ ትስስር እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን እንደሚያጠናክር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለስምምነቱ ትግበራ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ እና በኮሪደሩ አማካኝነት የጋራ ብልጽግናን እውን እንዲሆን የበኩሏን ድርሻ እንደምትወጣም አረጋግጠዋል።
በስምምነቱ አማካኝነት ቀልጣፋ የሎጂስቲክስ አገልግሎት፣ ትብብሩ እንዲጠናከር እና ለሀገራቱ መጻዒ ጊዜው ብሩህ እንዲሆን የሚያስችል መንገድ ከፍተናል ብለዋል ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026