
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ ስምምነቱ ገቢራዊነት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።
ለሁለት ቀናት በጅቡቲ የተካሄደው የኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን ምስረታ የሚኒስትሮች መድረክ የጅቡቲ-ኢትዮጵያ-ደቡብ ሱዳን-ዩጋንዳ (DESSU) ኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ታሪካዊው ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ እና ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ንግድ፣ ትስስር እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን እንደሚያጠናክር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለስምምነቱ ትግበራ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ እና በኮሪደሩ አማካኝነት የጋራ ብልጽግናን እውን እንዲሆን የበኩሏን ድርሻ እንደምትወጣም አረጋግጠዋል።
በስምምነቱ አማካኝነት ቀልጣፋ የሎጂስቲክስ አገልግሎት፣ ትብብሩ እንዲጠናከር እና ለሀገራቱ መጻዒ ጊዜው ብሩህ እንዲሆን የሚያስችል መንገድ ከፍተናል ብለዋል ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026