የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ኢዜአ ሀገራዊ ዕቅዶችና አቅጣጫዎች በውጤታማነት እንዲፈጸሙ የሚሰራቸውን የይዘት ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሀገራዊ ዕቅዶችና አቅጣጫዎች በውጤታማነት እንዲፈጸሙ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሠራተኞች በቀጣይ ሶስት ዓመታት ተግባራዊ በሚደረጉ የመንግስት አቅጣጫዎች እና ውሳኔዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሂደዋል፡፡


በውይይቱም ባለፉት ዓመታት የሕዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ፣ የሀገርን የዕድገት አቅጣጫ ያመላከቱ እንዲሁም የብሔራዊነት ገዥ ትርክትን ማስረጽ የሚያስችሉ ታላላቅ ተግባራት መከናወናቸው ተገልጿል፡፡

የመንግስት ውሳኔዎችንና አቅጣጫዎችን በተመለከተ ገለጻውን ያቀረቡት የኢዜአ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ነጋሲ አምባዬ፤ በሀገር ደረጃ ባለፉት ዓመታት የሕዝቦችን አንድነት ለማጠናከር፣ የፖለቲካ ምህዳርን ለማስፋት፣ ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገትን ከማፋጠን አንጻር አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡


በመጪዎቹ ሶስት አመታትም የብሔራዊ ገዥ ትርክት እና የሰላም ግንባታን ውጤታማ የማድረግ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ጠቅሰው፤ የፍትህ ዘርፉን ከማሳደግ አንጻርም በቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እንደሚሰሩ አብራርተዋል።

የኢኮኖሚ ልማትን ከማፋጠን አኳያም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግና የወጪ ንግድን በማስፋት በኩል ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።

ማህበራዊ ብልጽግናን የሚያረጋግጡ የጤና፣ ትምህርት እና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮችን ውጤታማ የሚያደርጉ ስራዎች እንደሚሰሩም አብራርተዋል፡፡

ውጤታማ የዲፕሎማሲ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፤መርኸን እና እውነትን መሠረት ያደረጉ ስራዎች እንደሚጠናከሩም አንስተዋል፡፡


አስተያየታቸውን የሰጡ የተቋሙ ሰራተኞች ኢዜአ መንግስት በአቅጣጫና ውሳኔ ያሳለፋቸው ነጥቦች ተገንዝቦ በመስራት ለስኬታማነታቸው የበለጠ ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ በሰጡት ማጠቃለያ ሃሳብ የተቋሙ ሰራተኞች የመንግስትን አቅጣጫዎችን ተገንዝቦ በመስራት ሀገራዊ ሃላፊነትን በብቃት መፈጸም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

መንግስት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ እያከናወናቸው የሚገኙ ሁሉን አቀፍ አቅጣጫዎችን በማሳካት በኩል የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.