የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በሸገር ከተማ አስተዳደር 502 ሞደል አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት ተሸጋገሩ  </p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ዙር 502 ሞደል አርሶ አደሮች ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ የኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ሃላፊ ሀይለሚካኤል አለሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የከተማ አስተዳደሩ አሰራሮችን ምቹ በማድረግ ባለሀብቶች በማኑፋክቸሪንግ፤ በአገልግሎት አሰጣጥና በግብርና ዘርፎች ተሰማርተው እንዲያለሙ የኢንቨስትመንት ቅበላ እያደረገ ይገኛል።

በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ዙር 502 ሞዴል አርሶ አደሮችን ወደ ኢንቨስትመንት ማሸጋገሩን ገልጸው፤ ይህም አርሶ አደሮቹ በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ውስጥ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ያስችላል ብለዋል።

በዚህም በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው ከ25 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጠርላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩ በግብርናው ዘርፍ ለአከባቢው አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ቅድሚያ በመስጠት ባላቸው እውቀትና ልምድ በዘርፉ እንዲያለሙ ማድረጉንም አስታውቀዋል።

በዚህም በኢንቨስትመንቱ ህብረተሰቡን የስራ እድል ተጠቃሚ በማድረግ በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሏል።

በከተማው ባለፉት ሁለት ዓመታት የኢንቨስትመንት ቅበላው በተለያዩ ምክንያቶች የቆመ ቢሆንም የአካባቢውን ሞዴል አርሶ አደሮችን በልዩ ሁኔታ እየተቀበለ መቆየቱን ተናግረዋል።

በዚህም 273 ሞዴል አርሶ አደሮቹን ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩ ማድረጉን አስታውቀዋል።

ሸገር ከተማ እንደ አዲስ ከመመስረቱ በፊት በኢንቨስትመንት ውጤታማነት ምጣኔ 44 በመቶ ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት ወደ 54 በመቶ ማደግ መቻሉን አክለዋል ሀላፊው።

በከተማው ወደ ኢንቨስትመንት እየተሸጋገሩ ያሉ ባለሀብቶች በውጤታማነት ላይ ትኩረት በማድረግ መስራት እንዳለባቸው አሳስበው የወሰዱትን መሬት በተሰጣቸው ጊዜ ውስጥ አልምተው የስራ እድል በመፍጠር በኢኮኖሚው ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.