
አዲስ አበባ፤የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፦በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት የበልግ አብቃይ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ይጠበቃል ሲል የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ በኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ለዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች እንደሚጠናከሩ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በደቡብ፤ በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ በመካከለኛዉ፣ በደቡብ ምዕራብ እንዲሁም በስምጥ ሸለቆና አጎራባች አካባቢዎች የተሻለ ጥንካሬ ይኖራቸዋል ብሏል።
በዚህም የበልግ አብቃይ አካባቢ በሆኑት የመካከለኛው፣የሰሜን ምስራቅ፣ የደቡብ ምዕራብ እና የደቡብ የሀገሪቱ አካባቢ ያሉ በርካታ ቦታዎችን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ተጠቁሟል።
አልፎ አልፎ በሚጠናከሩ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በደቡብ፤ በመካከለኛው፣በሰሜን ምስራቅ እና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ትንበያው አመላክቷል።
በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ላይ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ35 እንዲሁም በጥቂት ስፍራዎቻቸው ላይ ከ40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ተገልጿል።
በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት በሰሜን ምስራቅ፣ በመካከለኛዉ፣ በደቡብ እና በምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሚጠበቀው እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት ለበልግ የእርሻ ስራ እንቅስቃሴ አዎንታዊ ጠቀሜታ እንዳለው ተጠቁሟል።
በልግ ተለዋዋጭ ባህሪ ጋር ተያይዞ የሚኖሩት ደረቅ ሰሞናት እና ከፍተኛ የትነት መጠን የአፈር ውስጥ እርጥበት እጥረት እንዲኖር እንደሚያደርግ ተገልጿል።
አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች እና የሚመለከታቸው አካላት በሚሰጡ የግብርና ምክረ ሃሳብ መሰረት የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን ማከናወን እንዳለባቸውም ተጠቁሟል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026