
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት በኢነርጂ ዘርፍ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ከለውጡ ወዲህ በኢነርጂው ዘርፍ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ብሎም የጸሐይ ኃይል ማመንጫዎችን ከማስፋፋት አኳያ እና በሌሎችም አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን አክለዋል፡፡
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከለውጡ ወዲህ የኃይል ማመንጨት አቅምን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት በለውጡ መንግስት ልዩ ክትትል አሁን ያለበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ በልዩ ጥበብና ብልኃት መመራቱን ጠቁመዋል፡፡
በኢትዮጵያ በኢነርጂው ዘርፍ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ከጠቅላላ የህዝብ ብዛት 54 በመቶ የሚሆኑት የኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህም ከለውጡ ወዲህ ከ6 በመቶ በላይ ዕድገት ማሳየቱንም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች የሚያደርጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ዘርፉ በአመርቂ የዕድገት ደረጃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢነርጂው ዘርፍ ከ5 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ቆጣሪ ያላቸውን ደንበኞች ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ሀገር ኃይል የማመንጨትና የማቅረብ አቅም እያደገ መምጣቱን አንስተዋል፡፡
በማመንጨት አቅም እንደ ሀገር ታላቅ ስኬቶች መመዝገባቸውንም የገለጹት ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት ከ320 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞች መገኘታቸው ተናግረዋል፡፡
ከዋናው መስመር የራቁ አካባቢዎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በጸሐይ ኃይል መማንጫ ሶላር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በሶማሌ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ዳሰነች አካባቢዎችን ከ10 ሺህ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የጸሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በትምህርት ተቋማትና በሌሎችም የማዳረስ ስራዎች ላይ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026