የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በኢነርጂ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት በኢነርጂ ዘርፍ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ከለውጡ ወዲህ በኢነርጂው ዘርፍ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ብሎም የጸሐይ ኃይል ማመንጫዎችን ከማስፋፋት አኳያ እና በሌሎችም አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን አክለዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከለውጡ ወዲህ የኃይል ማመንጨት አቅምን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት በለውጡ መንግስት ልዩ ክትትል አሁን ያለበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ በልዩ ጥበብና ብልኃት መመራቱን ጠቁመዋል፡፡

በኢትዮጵያ በኢነርጂው ዘርፍ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ከጠቅላላ የህዝብ ብዛት 54 በመቶ የሚሆኑት የኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ይህም ከለውጡ ወዲህ ከ6 በመቶ በላይ ዕድገት ማሳየቱንም ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች የሚያደርጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ዘርፉ በአመርቂ የዕድገት ደረጃ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በኢነርጂው ዘርፍ ከ5 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ቆጣሪ ያላቸውን ደንበኞች ማፍራት መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

እንደ ሀገር ኃይል የማመንጨትና የማቅረብ አቅም እያደገ መምጣቱን አንስተዋል፡፡

በማመንጨት አቅም እንደ ሀገር ታላቅ ስኬቶች መመዝገባቸውንም የገለጹት ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ወራት ከ320 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞች መገኘታቸው ተናግረዋል፡፡

ከዋናው መስመር የራቁ አካባቢዎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በጸሐይ ኃይል መማንጫ ሶላር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህም በሶማሌ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ዳሰነች አካባቢዎችን ከ10 ሺህ በላይ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የጸሐይ ኃይል ማመንጫዎችን በትምህርት ተቋማትና በሌሎችም የማዳረስ ስራዎች ላይ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.