
ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል፡፡

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት በከተማው እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ እድገትና ለህዝቡ ተጠቃሚነት አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ነው፡፡
የኮሪደር ልማት ግንባታውን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ መጀመሩ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማት የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎች መዝናኛ ሥፍራዎችን ያካተተ በመሆኑ ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች መዝናኛነት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

በኮሪዳር ልማቱ የአካፋይ መንገድ፣ የመብራት ፖል ዝርጋታ፣ የካናል ስራ፣ የውሀ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ለልማቱ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ አንድ 1 አንድ 18 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026