የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው - አስተዳደሩ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ፡፡

በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል፡፡


ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት በከተማው እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ እድገትና ለህዝቡ ተጠቃሚነት አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ነው፡፡

የኮሪደር ልማት ግንባታውን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ለዚህም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ መጀመሩ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

የኮሪደር ልማት የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎች መዝናኛ ሥፍራዎችን ያካተተ በመሆኑ ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች መዝናኛነት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡


በኮሪዳር ልማቱ የአካፋይ መንገድ፣ የመብራት ፖል ዝርጋታ፣ የካናል ስራ፣ የውሀ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

ለልማቱ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡

በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ አንድ 1 አንድ 18 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.