ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል፡፡
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት በከተማው እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ እድገትና ለህዝቡ ተጠቃሚነት አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ነው፡፡
የኮሪደር ልማት ግንባታውን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ መጀመሩ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማት የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎች መዝናኛ ሥፍራዎችን ያካተተ በመሆኑ ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች መዝናኛነት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡
በኮሪዳር ልማቱ የአካፋይ መንገድ፣ የመብራት ፖል ዝርጋታ፣ የካናል ስራ፣ የውሀ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ለልማቱ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ አንድ 1 አንድ 18 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025