የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የገቢ መሰብሰብ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ማሳደግ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።

ኮንፍረንሱ "የልማት ግቦችን ለመደገፍ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል።

ኮንፍረንሱን የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የአይኤምኤፍ ቀጣናዊ የቴክኒክ ድጋፍ ማዕከል የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ(አፍሪታክ) በጋራ አዘጋጅተውታል።

በኮንፍረንሱ ላይ የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ11 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተወከሉ የዘርፉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የገቢና ፋይናንስ ባለሙያዎችና አማካሪዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙም በመረጃው ተመላክቷል።

የልማት ግቦችን መደገፍ የሚያስችልና የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከር የከንፍረንሱ ዋና ዓላማ መሆኑም እንዲሁ።

ቀጣናዊ ኮንፍረንሱ እስከ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ እና ከሁነቱ ጎን ለጎን የተሳታፊዎች የጉብኝት መርሃ ግብር እንደሚካሄድ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.