ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ አስፋልት መንገድ ግንባታን በማፋጠን በጥራት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።
የመንገዱ ግንባታ ያለበትን ሁኔታ የአማራ ክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራር አባላት ዛሬ ጎብኝተዋል።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ተስፋዬ አንተንይስሙ እንደገለጹት፤ የመንገዱን ግንባታ በጥራት በማከናወነ ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ ነው፡፡
ሆኖም የወሰን ማስከበር፣ የውሃ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ያጋጠሙ ጥቃቅን ክፍተቶችን ለማስተካከል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ይህም ጥረት ከክልሉ፣ ከደቡብ ወሎ ዞንና ከአካባቢው አመራር አባላትና ህብረተሰቡ ጋር በመነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት መንገድ የፕሮጀክት ተጠሪ መሃንዲስ ኢንጅነር ፀጋ ፈንታሁን በበኩላቸው፤ 74 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ግንባታ ሥራ ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ የመንገዱ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 39 በመቶ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ግንባታው በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ እየተደረገ ባለው ጥረት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።
የአማራ ክልል የርዕሰ መስተዳድሩ የመሰረት ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተሰራ ነው።
ከሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ወሰን ማስከበርና ሌሎች ያጋጠሙ ጥቃቅን ክፍተቶችን ለማስተካከል እንደሚሰራም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጋሻው አወቀ በበኩላቸው፤ የመንገዱ ግንባታ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብለዋል።
ግንባታው በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ህብረተሰቡ የበኩሉን ተሳትፎ እንዲያጠናክር መልዕክት አስተላልፈዋል።
ህብረተሰቡን በማወያየትና በማሳመን መንገዱ የሚያልፍበትን ቦታ ከሶስተኛ ወገን ነጻ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን ናቸው።
በጉብኝቱ የክልል፣ የደቡብ ወሎ ዞንና የሐይቅ ከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025