አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ):- የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሯ ከአምባሳደር ጁንግ ጋር ኢትዮጵዮጵያ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ዘመናትን የተሻገረ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት እንደሆኑም አውስተዋል።
በውይይቱ በክህሎት ልማት እንዲሁም የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ከመግባባት ላይ መደረሱን አመልክተዋል።
ኮሪያ ሪፐብሊክ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ለኢትዮጵያ ጠንካራ ድጋፍ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ገልጸው ይህም ትብብሩን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
ሚኒስትሯ ለአምባሳደር ጁንግ የሀገራቱን የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025