
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ):- የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሯ ከአምባሳደር ጁንግ ጋር ኢትዮጵዮጵያ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ዘመናትን የተሻገረ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት እንደሆኑም አውስተዋል።
በውይይቱ በክህሎት ልማት እንዲሁም የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ከመግባባት ላይ መደረሱን አመልክተዋል።
ኮሪያ ሪፐብሊክ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ለኢትዮጵያ ጠንካራ ድጋፍ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ገልጸው ይህም ትብብሩን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
ሚኒስትሯ ለአምባሳደር ጁንግ የሀገራቱን የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026